ማ ራ ና ታ !
ቅ ፅ 1
ቁ ጥ ር
2
ሴ ፕ ቴ ም በ ር
/
2 0 1 1
በሴንት ልዩስ መድኃኒዓለም ወንጌላዊት ቤ/ክ በየሦስት ወሩ የሚታተም መጽሔት
ልዩ ዕትም
ማ ራ ና ታ ኢ የ ሱስ ቶ ሎ ና !
ፓስተር ዶ/ር ተስፋ ወርቅነህ
ዘ ማሪ ሒሩ ት በ ቀ ለ ሒሩ ዘማሪ
ት በቀለ
2011 18ኛው የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት
ኮንፍራንስ ዴቪስ ፤ ኦክላሃማ (ኦገስት 11 - 14)
ፓ/ር አሰፋ ዓለሙ ካንሳስ
ፓ/ር በድሉ ታንቁ ዳላስ
ፓ/ር ተስፋ ወርቅነህ ሒውስተን
ፓ/ር ገነቱ ይግዛው ቺካጎ
እረኞቻችን!
ፓ/ር አበራ ምትኩ ኧርቪንግ
ፓ/ር እንድርያስ ሐዋዝ ሚኒሶታ
ፓ/ር ተስፋዬ ስዩም ሴንት ልዩስ
መልሕቅ
ፓ/ር ጳውሎስ ጉልላት ኦስተን
ገ ጽ3
ማራናታ!
አዘጋጅ ፦ ብርሃኔ ሞገስ ፅጌ
ፃፉልን፦
ካሜራ ፦ ወንደሰን ግዛው ፊደል ወ/ሰንበት ኤዲተርያል ቦርድ፦ ሔኖክ ገርቢ ታዲዮስ ማንደፍሮ አማኑኤል ገ/ሕይወት በለጠ መኩሪያ ወጁ ወራቦ ታሪኩ ገለታ ኮምፒዩተር ፅሁፍ ረዳቶች
melhiq@rwecstl.org
Melhiq Magazine 9116 Lack land Rd. Overland, MO 63114 (314) 363 4626
ሰላማዊት ፍስኃ / ቅድስት ደስታ
የምስራቹ ቃል ለሰው ሁሉ ፤ ሁሉም ሰው ለምስራቹ ቃል ! በዚህ መጽሔት ውስጥ የሚሰፍሩት አስተያየቶች የፀሐፊያቸውን እንጂ የመጽሔት ክፍሉንና የቤተ ክርስቲያኗን አቋም ላያንፀባርቁ ይችላሉ።
ተ.ቁ
የውስጥ ገጾች
ገጽ
1
ርዕሰ ጉዳዮቻችን
4
2
ከመጋቢዎች ምስባክ
ፓስተር ዶ/ር አሰፋ ዓለሙ
5
3
67 ደቂቃ ከዘማሪ ሒሩት በቀለ ጋር
6
4
ግንዛቤ ፦ ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ / ዶ/ር ምህረት ገ/ጻዲቅ
8
5
ከመፅሐፍ ቅዱስ ቃል ፦ ብፅዕት ድንግል ማርያም / ሰለሞን ለማ
10
6
መጣጥፍ ፦ የኪስ ቦርሳው / ብርሃኔ ሞገስ ፅጌ
12
7
ትኩረት፦ የነፍስ መልሕቅ / ታዲዮስ ማንደፍሮ
14
8
ጭውውት ከፓስተር ዶ/ር ተስፋ ወርቅነህ ጋር
20
9
ልዩ ዕትም 18ኛው የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ኮንፍራንንስ
26
“እርሱም እርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደሆነ እናውቃለን..” እናውቃለን..” ዮሐ 4:42
ገ ጽ4
ርዕሰ ጉዳዮቻችን እንደ አበሻነቷ ዘግይታ ብቅ አለች እንዳትሏት ። መጽሔታችን ልዩ ዕትም ያደረጋትን የኦክላሆማውን የሚድዌስት አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ አካትታ ለመምጣት ስትል ነውና መዘግየቷ ፤ ይቅርታዋን እያስቀደመች ፣ በድምፅ መቅጃ ተቀድታ፣ ምስሎቿ በፎቶ ካሜራ ተቀርጸውና ቦታ ቦታቸውን ይዘው፣ ቃላቶቿ በመተየቢያ ተተይበው ፣ ታርማ፣ አምራና አጊጣ እነሆ ልትነበብ በእጅዎ ገባች መልሕቃችን። እንዳልነውም በዛሬው ዕትሟ ከኦገስት 11 - 14 / 2011 መልሕቅ በዴቪስ ኦክላሆማ ፎልስ ክሪክ ኮንፍራንስ ማዕከል ( Davis, OK conference center) ከሚደረገው የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ላይ ተገኝታ የነበረውን ገጽታ ለአንባቢዎች ለመመስከር ሞክራለች። በፎልስ ክሪክ ኮንፍራንስ ማዕከሉ ታሪክ ጀምራ የዘንድሮውን ተካፋዮች የ72 ሰዓታት ቆይታ በስሱ ዳስሳለች። በውጭው ዓለም እየኖሩ አማርኛቸውን ከሚያቀላጥፉ ሕፃናትና ወጣቶች ጋር ተወያይታ፤ ልጆቻችችን አሳንሰን እንዳናያቸው የሚያስገነዝቡ ጭውውቶችንም ይዛለች። በዛ ያሉ የጉባኤው ተሳታፊዎችንና አጋልጋዮችንም አነጋግራ ለናሙና ያህል የምዕመናኑን በጌታ ያላቸውን የመረዳት ሁኔታ፣ የቤተሰብ ሁኔታ፣ የሀገር ቤት መኖሪያቸውን ፣ የአሜሪካ አመጣጣቸውን ስለኮንፍራንሱ ያላቸውን ጠንካራና ደካም ጎን በመዳሰስ ለመጭው ኮንፍራንሶች የተሻለ ዕቅድ ለመንደፍ በመጠኑ የሚረዱ መረጃዎችን ሰብስባለች። የሚድ ዌስት አብያት ክርስቲያናት ኮንፍራንስ ዓላማው አባሎች እንዲቀራረቡና ኅብረት እንዲኖራቸውም ነውና ይህንን ትልቅ ቤተሰብ እርስ በርስ ለማስተዋወቅ፣ አስተሳሰቦችን ለማለዋወጥ ፣ የኮንፍራንሱ መንፈስ እንዳይበርድ መረጃዎችን ለማቀባበልና የነበሩትን ሁኔታዎች ለማስታወስ እነሆ የሚድ ዌስት መገናኛ ድልድይ መሆኗን ጀምራለች። ግማሽ ክፍለ ዘመን በጌታ ቤት የኖረው ፓስተር ዶ/ር ተስፋ ወርቅነህ የዚህ ዕትም አንደኛው እንግዳችን ነው። አንጋፋው ወንጌላዊ በሕይወቱ ዙሪያ እንዲያናግረን የጠየቅነው እዚያው የኮንፍራንሱን ሂደት አመራር በሚሰጥበት ጥድፊያ ውስጥ ቢሆንም ፤ ሳያቅማማ ተወልዶ ካደገባት መርካቶ ኳስ ሜዳ እስከ ሒውስተን ቴክሳስ ያለውን ሕይወቱን አካፍሎን ለኅትመት አብቅተነዋል። ከውስጥ ገጾች ያገኙታል። አዘጋጇ ሀገር ቤት ሄዶ በነበረበት ወቅት ለኅትመት የሚመጥኑና ጌታ ይከበርባቸዋል የሚባሉ ግለሰቦችን ለማግኘት ጥረት አድርጎ ቃለ ምልልስ ካደረገላቸው ጥቂት ወገኖች መካከል የመጀመሪያዋን ዘማሪ ሒሩት በቀለን ይዘንላችሁ ቀርበናል። ዘማሪ ሒሩት በቀለ በሯን ከፍታ ከፍቅር መስተንግዶ ጋር ያላትን ምስክርነት ሁሉ ዘርግፋልናለች። አንዱን አስደናቂ ምስክርነት ባንዱ ላይ እየደራረበች እንዴት እንዳስደመመችን ከፅሁፉ ይከታተሉ። የመጽሔታችን አምደኛ ሰለሞን ለማ ከካሊፎርኒያ - “ ብፅዕት ድንግል ማርያም” በተሰኘ ርዕስ ስለ ጌታችን እናት ስለ ቅድስት ማርያም የሚለው አለው። ይህንን ውስብስብ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሀሳብ በባለጸጋ ቃላቶቹ በቀላል አቀራረብ ከሽኖልናልና ያጣጥሙት። ዶ/ር ምህረት ገ/ፃዲቅ “ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ” በሚል ርዕስ ምርጥ የፍልስፍና ጽሁፍ አቅርቦልናል። ከራሱ ሕይወት ጋር እያዋዛ ጭብጥ ዕውቀት የሚያቋድሰን ፀሃፊው አይናችን ስር የተቀመጠንና የማናየውን ነገር እንድናስተውልና አንዳንዴም በመደነቅ አፋችንን የሚያስዘንን ፣ የብሩህ አዕምሮ ውጤት የሆኑትን መረዳቶችን ከብዕሩ አፍሶልናል። ይመርምሩት። የመጽሔታችን ኤዲተርያል ቦርድ አባል ወንድም ታዲዮስ ማንደፍሮ “መልሕቅ” በተሰኘ ርዕስ ስር የመጽሔታችንን ስያሜ ምንጩን የሚመረምር ፅሁፍ አቋድሶናል። ይሄ መንፈሳዊ ፋይዳውን የዳሰሰ ፅሁፍ መጽሔታችንን ስያሜ ከማብራራት አልፎ ተጨባጭ ግንዛቤም የሚያስጨብጥ ነውና ይቅሰሙት። የመጽሔታችን ቦርድ በውጭ ሀገርና በሀገር ቤት በእረኝነት የሚያገለግሉ መጋቢዎች ሀሳባቸውን የሚያጋሩበት አንድ ገጽ በመመደብ “ከመጋቢዎች ምስባክ” የተሰኘ ዓምድ ከፍቷል። የመጀመሪያውንም ዕድል ለሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ሊቀ መንበር ለፓስተር ዶ/ር አሰፋ ዓለሙ በመስጠት “ፍቅርና አንድነት” በሚል ርዕስ የላኩልንን መልዕክት እነሆ በሚቀጥለው ገጽ ላይ አስቀምጠነዋል ፤ ንባብዎን ይጀምሩበት። መልካም ንባብ ! መልሕቅ
ገ ጽ5
ማራናታ!
ከመጋቢዎች ምስባክ ፍቅርና አንድነት አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምር ፍቅርና አንድነትን ወይም ሕብረትን በማነጻጸር ይናገር ነበር። እርሱም “ፍቅር ትዕዛዝ ስለሆነ ስለፍቅር መጸለይ የለብንም ። ይሁንና ኢየሱስ ክርስቶስ በዮሐንስ አስራ ሰባት ላይ ስለአንድነት ወይም ስለሕብረት በመጸለይ ምሳሌውን ትቶልናልና ስለአንድነት ወይም ስለ ሕብረት መጸለይ ይኖርብናል!” ሲል ተናገረ። እውነት ነው “ፍቅር ስጠን” ወይም “እንድንዋደድ አድርገን ብሎ ወደ እግዚአብሔር መጸለይ እያወቁ አይንን በመጨፈን ጋደም ብሎ ተኝቻለሁ ቀስቅሱኝ!” እንንደማለት ስለሚሆን እንዲያው መገበዝ ነው። ወደ አንድነት ወይም ወደ ሕብረት ፊታችንን ስንመልስ ከላም ወተት እንደሚወጣ አንድነት ወይም ሕብረት ከፍቅር እየታለበ የሚወጣ ወተት መሆኑን መዘንጋት የለብንም። ላም ከሌለ ወተት ከየት? ፍቅርስ ከሌለ አንድነት ወይም ሕብረት እንዴትና ከየት? ስለሆነም እንደ ፍቅር ሁሉ ስለአንድነት ወይም ስለሕብረት መጸለይ እያወቁ አይንን ጨፍኖ በመጋደም ተኝቻለሁ እንደማለት ሊሆን አይችልምን? ኤፌሶን 4፦3 ላይ “በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት(ሕብረትን) ለመጠበቅ ትጉ” ይላል እንጂ ጸልዩ አይልም። አንድነት ወይም ሕብረት የሚሠራ ከተሠራም በኋላ የሚጠበቅ እንጂ የሚጸለይበት ጉዳይ አይደለም። ፓስተር ዶ/ር አሰፋ ዓለሙ
ዛሬ የኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት በሀገር ውስጥ ሆነ ከሀገር ውጭ አንድነትን ወይም ሕብረትን ለመሥራት ሆነ ለመጠበቅ የተቸገሩበት ግዜ ነው። አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መሬት ላይ እንደወደቀ ሸክላ ብትንትናቸው እየወጣ ነው። አስተምህሮው ሆነ አሰራሩ ሌሎችም እዚህ ላይ መጥቀስ የማልሻቸው ነገሮች ለዚህ ሁኔታ በሰፊው አስተዋጽዖ እያደረጉ ነው። ይሁንና በእንዲህ ያለው ቀውጢ ግዜ የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ላለፉት አስራ ስምንት ዓመታት አዎንታዊ ለውጥ በማምጣት እየታገለ ይገኛል። ሚድ ዌስት በ1995 ዓመተ ምኅረት በሒውስተን ፣ በዳላስና በካንሳስ አብያተ ክርስቲያናት እረኞች በሒውስተን ከተማ ላይ የመሠረቱን ድንጋይ አስቀመጠ። ዓላማው ከሰዓት ወይም ከግዜ ዞን ሳይወጣ በዚያው ዞን ውስጥ ያሉትን አብያተ ክርስቲያናት በማካተት ወጥ ትምህርቶችን ለማስተማር፣ ለአገልጋዮች ሴሚናሮችን ለማዘጋጀት፣ ኑፋቄዎችንና መናፍቃንን ለመቋቋም ፣ መከፋፈልን ለመግታት፣ አገልጋዮችን ባስፈለገ ግዜ ለመለዋወጥና አመታዊ ኮንፍራንስ አብሮ ለማካሄድ በተለያየ አካባቢ የነበረውን ምዕመን በአካል ተገናኝቶ እንዲተዋወቅ ለመርዳት ነበር። ዓመታዊ ኮንፍራንሱ በአስራ ሰባት ዓመታት 18 ግዜ ተደርጓል። በሦስት አብያተ ክርስቲያናት የተጀመረው ሕብረት ዛሬ ወደ ስምንት ደርሷል። የወደፊት ሕይወቱ ደግሞ በእግዚአብሔር እጅ ነው። ካንዳንድ ሁኔታዎች እንደተረዳነው አማካይ ቦታ ከተገኘ ወደዚህ ሕብረት ለመቀላቀል የማያወላዱ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት እንዳሉ ነው። ይህ ሕብረት በዓይነቱም ቢሆን በአሠራሩ በአሁኑ ግዜ በሀገር ውስጥ ሆነ ከሀገር ውጭ በኢትዮጵያውያን መካከል በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው። ኮንፍራንሱን በተመለከተ የተሳታፊው ብዛት ከዓመት ዓመት ሲጨምር ይታያል። በሌላ በኩል ደግሞ በሚሰጡት መስመር ያልለቀቁ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርቶች የብዙዎች ሕይወት ተለውጦበታል። በልዩ ልዩ ደዌ የተያዙ ብዙዎች ሲፈወሱ ፤ ከአጋንንት፣ ከተለያዩ አልባሌ ባሕሪያትና እሥራቶች በጌታ ኢየሱስ ስም ነፃ ወጥተዋል። ብዙዎች ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ ሲጠመቁ ታይቷል። ኮንፍራንሱ የአዋቂዎች ፣ የወጣቶችና የሕፃናት በመባል የተከፈለ ሦስት አካል አለው። የ2011 ዓመተ ምሕረትን ኮንፍራንስ ከሌሎች ለየት የሚያደርገው የአዋቂዎቹ ፕሮግራም በዌብሳይት ( በኢንተርኔት) ቀጥታ ለመላው ዓለም መተላለፉ ነው። ክብር ሁሉ ለእግዚአብሔር ይሁን ። ሚድዌስት የአብያተ ክርስቲያናት ሕብረት እንጂ ሚኒስትሪ እንዳልሆነ በዚህ ላንባቢዎች ማሳሰብ እወዳለሁ። የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ሊቀመንበር ፓስተር ዶ/ር አሰፋ ዓለሙ
ገ ጽ6
67 ደቂቃዎች ከዘማሪ ሒሩት በቀለ ጋር
ከዛሬዋ የመልሕቅ እንግዳ ጋር ከሚያገናኘኝ ወንድምጋ የነበረን የቀጠሮ ሰዓት እጅግ ስላለፈ ተስፋ ቆርጬ፣ ከቤቴ ወጥቼ ቦሌ መንገድ ላይ ኦሎምፒያ ከሚባለው አካባቢ ከሚገኝ አንድ ካፌ በረንዳ ላይ ሻይ ይዤ ቁጭ ብያለሁ። ከሀያ አመታት በላይ በውጭ መቆየቴ ለዚህ ላደግኩበት ሰፈር ፍጹም ባይተዋር አድርጎኝ ወጭ ወራጁን እንደ ቱሪስት በመቃኘት ተጠምጃለሁ። የሰዉንና የመኪናውን ግርግር ሳይ ልጅ ሆነን እዚህ መንገድ ላይ በየ10 ደቂቃው ብቅ በሚሉት መኪናዎች ታርጋ “ሞላ ጎደለ” የምንጫወተው ነገር ከአዕምሮዬ ይመጣና ለውጡ ግርም ይለኛል። አዎ አሁን ዘመን ተለዋውጧል ። ከተማውም ፣ ሀገርም፣ ሕዝቡም ሳይቀር ተቀያይሯል። እኔም እንደዛው አልኩ በልቤ። አፍታም ሳልቆይ “ያችስ ሰው?” የሚል ጥያቄ አጫረ አዕምሮዬ። ያች ሰው ያልኩት ከዚህ ከኦሎምፒያ ትንሽ ወረድ ብሎ መስቀል አደባባይ ከሚባለው ቦታ ላይ ድሮ ሕጻን ሆኜ የፖሊሱ የሙዚቃ ኦርኬስትራ አስተዋዋቂ ካሳሁን ገርማሞ “......የቀኑ ዝቅተኛ ሙቀት እከሌ ድግሪ ሴንቲግሬድ የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ሒሩት ድግሪ ሴንቲግሬድ! የፖሊስ ሰራዊት ኦርኬስትራ በመስቀል አደባባይ አካባቢ ፀሐያማ ሆኖ ይውላል!” እያለ በከፍተኛ ዕውቅናና በኩራት ሲያስተዋውቃት የነበረችውን ሒሩት በቀለን ማለቴ ነው። ቀጠሮዬ ከሷ ጋር ቃለ ምልልስ ለማድረግ ነበርና ለዚያ ሳይሆን አይቀርም ወደ አዕምሮዬ የመጣችው። እሷማ በመንፈሳዊ ሕይወቷ ፍጹም መለወጧን ከሰማሁ ሰንብቻለሁ። በጆሮዬ የሰማሁትን በአይኔ አይቼ ላጣጥመው ነው ችኮላዬ። ያ ብቻ አይደለም ለናንተ ለአንባቢዎች የማጋራው ምስክርነት ለመቋጠርም ጓጉቻለሁ። ጉጉቴ መና ሆኖ አልቀረም ያ በስልክ ብቻ የማውቀው ከዘማሪ ሒሩት የሚያገናኘኝ ወንድም ደወለ። ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት እንደዘገየ ነግሮኝ “ምን ቢመሽ ዛሬ ሳላገናኝህ አላድርም” ብሎ እዛው ኦሎምፒያ እንድጠብቀው ነግሮኝ ሲበር መጣ። የድምጽ መቅጃዬን ከቤት ያዝንና ከቦሌ መንገድ ቁልቁል ወደ አስመራ መንገድ ( ኃይሌ ገ/ሥላሴ ጎዳና) ከዛም ወደ ባምቢስ ታጥፈን ውስጥ ውስጡን ነድተን የኡራኤልን ድልድይ ተሻገርንና ብዙም ሳንርቅ ግራና ቀኝ ታጥፈን ከሒሩት መኖሪያ ቤት ደረስን። ከረጅሙ ግምብ አጥር ውስጥ የብረት በሩ ተከፍቶልን ስንገባ ጸጥ ረጭ ያለው ግቢ የአዕምሮ ሰላምን ያሰፍናል። በውስጥ በኩል ከግንብ አጥሩ ላይ የተቀረፀውን ትልቅ መስቀልና “ኢየሱስ ጌታ ነው!” የሚለውን ቃል ሳነብ ሒሩት ምን ያህል በጌታ እንደተለወጠች ሹክ አለኝ። ወደ ውስጥ ገብተን ወንበር እንደያዝን በእኔ አዕምሮ መዝገብ ቤት ውስጥ ያለውን የድሮ ፎቶግራፏን ከግድግዳ ላይ አስተዋልኩት። ብዙም ሳትቆይ ሒሩት ረጅም ቀሚሷን አድርጋ ሰማያዊ ተከፋች ሹራቧን ደርባ ቀይ መጽሐፍ ቅዱሷን አንግባ ኮቴዋም ሳይሰማ ከጓዳ ውስጥ ብቅ አለች በፈገግታ። መድረክ ላይ ካየኋት ብዙ ከመቆየቱ አኳያ “በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለችው” አልኩኝ ለራሴው። የትውውቅ ሰላምታ ከተለዋወጥን በኋላ ወዲያው ቃል ማካፈል ጀመረች። “ዝም እንበል” በሚል ርዕስ ከመጽሐፈ ነገስት ካልዕ 4፡8 ቃል ከማካፈሏ በፊት “ አንተን ጠርቶ ያፈረ ማን አለ? ኧረ ማን አለ? “ የሚለውን መዝሙር አዘመረችን። ሰርጀሪ በነበርኩበት ግዜ ጌታ እንዴት ከኔ ጋራ እንደነበረ ለመመስከር ነው ከዚህ መጽሔት ጋር ቃለ ምልልስ ለማድረግ ፈቃደኛ የሆንኩት በማለት ከሆስፒታል ስትወጣ ጌታ የሰጣትን ዜማ ። አንተ ለኔ ጉልበት ፤ ሆነኽኝ ነው እንጂ አምላኬ ሆይ ! ያንን ሁሉ ችግር ፤ ያንን ሁሉ ቀንበር እኔስ እንዴት ችዬ? እሻገረው ነበር እንግዲህ አልፈራም ሰልፍም ቢነሳብኝ በመከራዬ ቀን ድንኳኑ ሸፈነኝ በዛ በጭንቄ ቀን መንፈስህ ሰወረኝ አዎ ድንኳንህ ሸሸገኝ ፤ ምኅረትህ መጣልኝ እያለች አዜመችና የዚህን መዝሙር መነሻ ታሪክ በቃለምልልሱ ውስጥ አቋደሰችን። እኔም ይህችን ተወዳጅና ድፍን ሀገር የሚያውቃትን ሰው ለማናገር ጌታ ስለከፈተልን በር አመሰገንኩት። ድምፀ መቅረጫዬንና አፌን ከፍቼ አዳመጥኳት። አስደናቂው ምስክርነቷ ያስደምማል፤ ብዙም ሳንገፋ ስለመሸ ዳግም ቀን ቀጥረን “በሰሊሆም የክርስቲያኖች ሬስቶራንት” ከባለቤቴ ጋር ምሳ ጋበዝናትና በፀሎት ቤትነትም ከሚጠቀሙበት ቢሮ ውስጥ ዳግም በሕይወቷ ዙሪያ ተወያየን። ድንቅ ሕይወቷ ማረከን። በጌታ የተገራው አንደበቷና ስነ ምግባሯ አስደነቀን። ስለ እርሷ ጌታን በእጅጉ አመሰገን። የሒሩትን ወደጌታ መመለስ ላጤነው ሰው በራሱ እጅግ ታላቅ ምስክርነት ነው። ጥላ የመጣችውን ዝና ፣ ንዋይ ፣ ዓለማዊ ደስታ ላየ ፈጥኖ ፈራጅ አለማዊ ሰው “አብዳ መሆን አለበት?” በማለት ብቻ የሚያልፈው ቢሆንም ፤ ልብ ያለው ሰው ግን “ምን አግኝታ ቢሆን ነው?” ብሎ መጠየቅና እሷ ያጣጣመችውን የጌታን ፍቅር ለመቅመስ መጣደፍ ያለበት ነው የሚመስለኝ። ስለዚች የእግዚአብሔር አገልጋይ ባርያ ወደ አሜሪካ ተመልሼ ድረ ገፅ ውስጥ ታሪኳን ስመረምር ሒሩትን በዘፋኝነት ለመውሰድ ምድርጦርና ፖሊስ ያደረጉት ፍጭት የሚገርም ነው። ታሪኩን መስካሪው ግለሰብ ፖሊስ እንዴት ኮንትራት እንዳስፈረማትና “ባልታወቀ ወንጀል” እንደተያዘች በማስመሰል በፈጥኖ ደራሽ ግቢ ውስጥ /በኋላ ኒልሰን ማንዴላ ለወታደራዊ ስልጠና መጥተው ለ6 ወር በኖሩባት ክፍል/ በጥበቃ ስር አቆይቶ ሙዚቃ እያለማመደ ለዘመን መለወጫ ከተመልካቹ ሕዝብ መካከል አውጥቶ በማዘፈንና ከዚያም ስትጨርስ ምድርጦሮች እንዳይነጥቋቸው መብራት አጥፍተው ሸሽገው ወደ ፈጥኖ ደራሽ በመውሰድ ሒሩትን ለ 30 ዓመታት እንዴት የራሳቸው እንዳረጓት ተርከዋል። እግዚአብሔር አምላክ ደግሞ በተራው የናንተም አይደለችም ብሎ ከፖሊሶች ላይ ተረክቦ፤ ለውጦና አዲስ ሰው አድርጎ ሲገለገልባት እነሆ ዓመታት ተቆጠሩ። የስራ ባልደረቦቿ በዓለም በነበረችበት ግዜ “በስነምግባሯ የተወደደች፣ለዛ ያላት ጥርስ የማታስከድን ቀልደኛ ፣ ለጭፈራና ዳንኪራ የማትመች መልዕክት ያላቸው ለስላሳ ሙዚቃዎችን ብቻ የምትጫወት ነበረች” ብለው ቢመሰክሩላትም ሒሩት ግን ጠንቋዮች እንኳን እሷን የበለጠ ኃጢያተኛ በማድረግ “ሒሩትን ይቅር ያለ አምላክ እኔንም ይቅር ይላል” እያሉ ጌታን እንዳገኙ ከሰዎች እንደተመሰከረላት ነግራናለች። ከዚች የጌታ ባሪያ ጋር ያደረግነውን ሙሉ ቃለ ምልልስ እንዲያነቡ የምንጋብዝዎ እንግዳችንን ጌታ ይባርክሽ! በማለት ነው።
መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የት የት ነው የሚኖሩት ልጆችሽ? መልሕቅ፦ እስቲ ስለ ውልደትሽና ቤተሰብሽ ትንሽ አጫውቺን? ሒሩት፦ ሒሩት ፈሪሃ እግዚአብሔር ከነበራቸው ወላጆች አዲስ አበባ ቀበና አካባቢ ነው የተወለድኩት። አንድ እህትና አንድ ወንድም አለኝ። ወንድምና እህቴ እነዚህ ብቻ ሲሆኑ ጌታ የሰጠኝ ግን ብዙ እህቶችና ወንድሞች አሉኝ።
መልሕቅ፦ የት ተማርሽ? ሒሩት ቀበና አድቬንቲስት ሚሲዮን ነው ትምህርቴን የጀመርኩት፣ በኋላም ከቤተሰቤ ጋር ተዛውሬ አሰላ ራስ ዳርጌ ት/ቤትም ተምሬያለሁ።
መልሕቅ፦ ስንት ልጆች አሉሽ? ስንቶቹ ወንዶች ስንቶቹ ሴቶች ናቸው? ሒሩት፦ ሒሩት 7 ልጆች ነው የወለድኩት። ሴቶቹ ሶስት፣ ወንዶቹ አራት ናቸው። እግዚአብሄር ይመስገን! ግማሾቹ ወልደዋል።
መልሕቅ፦ አያት ሆነሻል ማለት ነዋ? ሒሩት፡ሒሩት፡- አዎ! እግዚአብሄር ይመስገን!
ዘማሪ ሒሩት በቀለ
ሒሩት፦ ከፊሎቹ እዚህ ኢትዮጵያ ከፊሎቹ አሜሪካ ነው የሚኖሩት። መልሕቅ፦ ወደ ስራ ዓለምስ እንዴት ገባሽ? ሒሩት፦ በልጅነቴ ማንጎራጎር እወድ ነበርና ሳንጎራጉር የሰማኝ አንድ የጎረቤቴ ልጅ “ዘፈን ስትዘፍኚ እሰማሻለሁ፣ ጥሩ ድምጽም አለሽ፣ ለምን ስራ አላስገባሽም” ብሎ ምድር ጦር ሙዚቀኛ ወስዶ አስቀጠረኝ። መልሕቅ፦ ከዛስ ምን ተፈጠረ? ሒሩት፦ እዚያ ቦታ ስሄድ እንዲህ ታዋቂ እሆናለሁ ብዬ ማሰብ ይቅርና ቤተሰቦቼ እንኳን ሳያውቁ ተደብቆ የሚሰራ ስራ መስሎኝ ነበር። ያኔ ልጅነትም ስላለ ማመዛዘኑም አልነበረም። ሰው ፊት እንደምቀርብም አላወቅኩም ነበር። ብቻ ዝም ብዬ ሄጄ ተቀጠርኩ። አለቆቻችንም ልጆች ስለነበርን የፍቅር ዘፈን አይሰጡንም ነበር።
ገ ጽ7
ማራናታ!
ስለሀገር ጉዳይና የመሳሰለ ነበር የሚሰጡን። ታዲያ ዜማው ተዘጋጅቶ ለማሳየት ብሄራዊ ቲያትር ሄድን ። በኔ ቤት ማንም የሰማ የለም ብያለሁ ፤ ነገር ግን እኔ ሳላውቅ እናቴም ለካስ ገብታ ነበር። አስተዋዋቂው ሒሩት በቀለ “የሐር ሸረሪት” የተባለውን ዜማዋን ታቀርባለች ብሎ አስተዋውቆኝ መድረክ ላይ ስወጣ አዳራሹ ጥቅጥቅ ብሎ በጣም የሚያስደነግጥና የሚያስፈራ ነበር። መዝፈን እንደጀመርኩ በማፈሬና በመደንገጤ ልወድቅ ደረስኩ። በኋላም ዝግጅታቸውን አበላሽቼ ሳልጨርስ ሮጬ ስለገባሁ ጓደኛዬ ተክታኝ ገብታ ጨረሰችው። “እንዴት ይሻላል ታዲያ በዚህ ዓይነት እንዴት ትዘልቀዋለች?”ተባለ። “አትፍሪ” ብለው ቢመክሩኝም በምክር የሚሆን ነገር አልነበረም። በኋላም ወደቤቴ ስገባ ቤተሰቤ በሙሉ ያለቅሱ ነበር። ለሙያው የተሰጠው ስም ጥሩ አልነበረም ያኔ፤ አዝማሪ ነበር የሚባለው። “የሞተውን አባትሽን ስሙን በመጥፎ አስነሳሽው” ተባለ። በመድረክ ላይ የተሰራው ዜማ በቅጽበት በሬዲዮ ስለተለቀቀ ልክዳቸው አልቻልኩም። “ምነው ልጄ ምን ሆንሽና ዘፈን አለም ውስጥ ገባሽ?” አሉ የአባቴ አባት አያቴ ። ስለተቀየሙም “ከኑዛዜ ውስጥ አውጥቻታለሁ” አሉ። /ሳቅ / ትንሽ ቆይቶ አንድ ልጅ መጥቶ ፖሊስ ሙዚቀኛ ብትገቢ ይሻልሻል ብሎ ወሰደኝና ለ7 ዓመት ኮንትራት አስፈረሙኝ። ፖሊስና ጦር ሰራዊት መፋጠጥ ጀመሩ። በመድረክ ላይ ይከራከሩ ጀመር፡፡ ክርክራቸው በቅርቡ “በፊት የተሰራ” ተብሎ በሚዲያ ወጥቶ ነበር። ያው ፖሊስ በዚህም በዚያም ብሎ አስቀረኝ። እዚያም በሙዚቃ አለም ውስጥ ለብዙ ግዜ ሰራሁ። ታዋቂ ለመሆንም በቃሁ። የሚገርምመው ነገር ግን እኔ ስለ ታዋቂነት ምንም የምደነቅበት ነገር አልነበረም። የእግዚአብሄር ስሙ ይባረክ! ያን ግዜም ቢሆን ፈሪሃ እግዚአብሄር በውስጤ ነበር። እኔ በምሰራበት አካባቢም በውጭም የምፈልገው ፍቅር ነው። ሴቷም እህቴ ወንዱም ወንድሜ እንዲሆን ነው ፍላጎቴ እንጂ ሌላ ነገር በውስጤ አላስብም ነበር። ይሄን ያደረገው እግዚአብሄር ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ አንድ ሰው መጥቶ መሰከረልኝ። እሱም ከኛ ጋር ይሰራ የነበረ መሳሪያ የሚጫወት ሰው ነው። መልሕቅ፦ ስሙ ማን ይባላል? ሒሩት ፦ አለሙ በቀለ ይባላል። ቤት ድረስ መጥቶ ፍርጥ ያለ ምስክርነት መሰከረልኝ ...”አሁን አንቺ ማጌጥሽን፣ ውጭ አገር መሄድሽን፣ ሰው ተደሰተ ብለሽ ማለትሽን እንጂ ነፍስሽ የት እንደምትገባ አታውቂም” አለኝ። “እንዴት የት ትገባለች? ..ወደ እግዚአብሄር ነዋ የምትሄደው” አልኩት። አይደለም ጌታን ካልተቀበልሽ እንደሱ አይሆንም” አለና በጣም በሚያስደነግጥ ሁኔታ ነገረኝ። “ ያለሁበት ስፍራ አይመችም ...ጌታን ተቀብሎ ደግሞ መዝፈን አይቻልም ታዲያ እንዴት አደርጋለሁ?” አልኩት። “እሱን ለሱ ተይው እሱ ራሱ ይፈታዋል ግዴለሽም” አለኝ። እናም ጌታን የግል አዳኜ አድርጌ ተቀበልኩ። መልሕቅ፦ በስንት ዓ/ም መሆኑ ነው? ሒሩት፦ በ1977 ይመስለኛል ነው ስንት ዓመት መሆኑ ነው? መልሕቅ፦ 26 ዓመት። ሒሩት፡ አዎ! በዚያን ግዜ ሀይለኛ የደርግ ስርዓት ስለነበር ተደብቄ ነበር የማገለግለው። ያኔ
እንዳሁኑ በነፃነት አናገለግልም። ጌታ ያስነሳልኝ ወገኖች እየወሰዱ “እንዲህ ዓይነት ቤት ውስጥ አገልግዪ” ይሉኛል። አገለግላለሁ። ...ስነሳ ጌታ ቀስ ብሎ ነው ያስነሳኝ። እኔ ብዙ ገጣሚ አይደለሁም በመሰረቱ እዚያ ደራሲ ነበረን። ጌታ አንድ አምስት ዜማዎችን ሰጥቶኝ በየቤቱ እየሄድኩኝ ያለ አጃቢ ሙዚቃ ብቻዬን እዘምር ነበር። እናም ይሄ መዝሙር በውስጤ እያደገ መጣ.... መልሕቅ፦ በየሰዉ ቤት እየሄድሽ በምትዘምሪበት ሰዓት ስራሽን አልተውሽም ነበር ማለት ነው? ሒሩት፦ አልተውኩም። ቢሆንም ጌታን ከተቀበልኩ በኋላ ፍቅሩ በውስጤ ስለገባ ለሙዚቃ ስራ ትክክለኛ ሰው አልነበርኩም። “ጌታ ሆይ እንዴት ሁለት የማይስማማ ነገር ባንድ ላይ ይሆናል?.... ምነው ዝም አልከኝ?” እያልኩ እፀልያለሁ። አምላክ ግን የራሱ ግዜ አለው። አንድ ቀን የሙዚቃ ስራ ልንሰራ አንድ ቦታ ወሰዱኝ። ይገርማችኋል ስንት ሺህ ሰው ነው ያለው እዚያ ቦታ ላይ፣ ልዝፈን ስለው ጠፋብኝ። ደነገጥኩ በጣም። ጠፋብኝ በቃ! ሙዚቃው ላ ላ ላ ይላል “ አዲስ አበባ ነው ቤቱ የሚል ሙዚቃ ነው አዲስ አበባ ቤቱ” ማለት ብቻ ሆነ .... ከዚያ ያለፈ መጫወት አልቻልኩም ። አለቃዬ እግዚአብሄር ይባርከው “አንድ ነገር ደርሶባት ነው እንጂ እሷ እንዲህ ዓይነት ሰው አይደለችም” አለልኝና ከጉድ አወጣኝ። ....ለካስ ነገሩ ተቆርጧል፣ የምዘፍንበት ሰዓት አልቋል ። በቃ! ከንቱ ነገር ላይ እንዳለሁ ራሴን አየሁት። ከዚያ በኋላ የአከርካሪ /spinal cord/ በሽታ ደረሰብኝና ለሕክምና አሜሪካ ሄድኩ። እነሱም ወረቀት ፃፉልኝ “መስራት አትችልም” ብለው። በዛ ምክንያት ከፖሊስ ተሰናበትኩ። ብዙ ግዜ ሆነኝ ከሙዚቃ ዓለም ከወጣሁ። በጣም ብዙ። በ19.....እ እ እ ይቅርታ ዘመኑ ጠፋብኝ። / ከሌላ ምንጮች በ1981 እንደሆነ ተረድቻለሁ/ መልሕቅ፦ ከዚያ የትኛው ቤ/ክ ትካፈዪ ጀመር? ሒሩት፦ መሠረተ ክርስቶስ ምስራቅ አጥቢያ ነበር የምካፈለው። ነገር ግን ሰፈሬ ውስጥ የመሠረተ ክርስቶስ ቻፕል ከተከፈተ ጀምሮ እዚሁ በቅርብ ቦታ እካፈላለሁ። መልሕቅ፦ የቤተሰብሽ ሕይወት በጌታ ምን ይመስላል? ሒሩት፦ ከፊሎቹ በጌታ ናቸው ከፊሎቹም ደግሞ የእግዚአብሄር ፈቃድ በሆነ ግዜ ይመጣሉ ብዬ አስባለሁ። አንድ ቀን ሰባቱም ልጆቼ ሙሉ በሙሉ ወደ ጌታ እንደሚመጡ እተማመናለሁ። እግዚአብሄር ይመስገን.... የቤተሰቤ ሁኔታ መልካም ነው። አመስጋኝ ብሆን እግዚአብሄር ለኔ ያደረገው በጣም ብዙ ነው። የቱን አንስቼ የቱን አስቀረዋለሁ? ሀሌ ሉያ! ስንቱንስ እመሰክረዋለሁ? ብዙ ነገር አድርጎልኛል። መልሕቅ፦ እስቲ ለሰው መመስከር የምትፈልጊው በቤተሰብሽ ውስጥ ጌታ ያደረገልሽ ነገር ካለ? ሒሩት፦ ያው በቤተሰቤ ውስጥ ብዙዎቹ ጌታን ማግኘታቸው እኮ ትልቅ ነገር ነው። ባለፈው ዘመን በዚች ምድር ላይ ብዙ ነገር ነበር። የነበረውን ሁኔታ ልገልፀው ባልፈልግም ከዚያ ሁሉ እሳት አወጥቶልኛል ልጆቼን፣
ቤተዘመዶቼን ....እግዚአብሄርን አምኜዋለሁ። እሱም አላሳፈረኝም። ጌታ ስሙ ይባረክ! ጌታዬን እወደዋለሁ! አከብረዋለሁ! ለዘላለምም እንድገዛለት ምኞት አለኝ! ሀሌሉያ! ስሙ ክቡር ይሁን ! እጅግ የተፈራ ነው። እኔም ሰው ሆኜ የሱ ባሪያ ልሆን በቅቻለሁ! እግዚአብሄር ይመስገን! ሁልግዜ እለዋለሁ ። ጌታዬን አከብረዋለሁ። ጌታዬ ፈጣሪዬ ብቻ ሳይሆን የማማክረው አባቴም ነው። በቃ! የሆነውን ሁሉ እነግረዋለሁ። እሱ ይፈጽማል። አንዳንዴ ነገሮች ሁሉ ፈጥነው ሲመጡ አይቼ “ጌታ ሆይ እንደዚህ ትሰማናለህ እንዴ እውነትም ?” እያልኩኝ እደነቃለሁ። መጨረሻዬን ያብጀው እግዚአብሄር። /አንዳንዴ ስለ ጌታ ምኅረትና ቸርነት ስታወራ ወዲያው በመንፈስ ትቀጣጠላለች። ቃለ ምልልስ የምታደርግ ሳይሆን በአምልኮ ላይ ያለች ትመስላለች/ መልሕቅ፦ የፀሎት ሕይወትሽስ እንዴት ነው? ሒሩት፦ መፀለይ በጣም እወዳለሁ ። በተለይ ብቻዬን በምፀልይበት ሰዓት ሁኔታዎችን ሳይ “ወየው ጉድ!” እያልኩ እደነቃለሁ። አሁንም የምመለከተው ያደረገልኝን ነው። መልሕቅ፦ አንድ ምሳሌ የምትስጪን አለ? የፀሎትሽ መልስ የሆነልሽ ነገር ሒሩት፦ ለኔ ያደረገልኝን ታላቅ ነገር በምችለው ደረጃ ልግለፀው። እግዚአብሄር ይረዳልኛል። የዛሬ ሁለት ዓመት ወደ አሜሪካ ሄጄ ነበር። እዛ ሄጄ እያለሁ ልጆቼ በሲቲ ስካን ( CT scan ) እንድታይ አደረጉ። የኩላሊት ጠጠር አለብሽ ተባልኩ። “እንዴ ታዲያ ካለ ለምን አያመኝም” አልኩ። ሰርጀሪ መሆን አለባት ተባለ። “ጌታ ሆይ! እንግዲህ ያንተ ፈቃድ ከሆነ ልሁን ያንተ ካልሆነ ይቅር” አልኩት ። የሱም ፈቃድ ሆነና ሆስፒታል ሄድኩኝ። ያስፈራል መቼም፤ ሰርጀሪ ( ቀዶ ጥገና ) ሆኜ ስለማላውቅ በጣም ፈራሁ። አስገቡኝና ከመቅጽበት ሁሉን ነገር አደረጉ። እኔ አኒስቴዥያው (ማደንዘዣው) በጭን ላይ ወይም በክንድ ላይ የሚወጋ መስሎኝ እጠብቅ ነበር። ለካስ በአይ ቪ ( IV Fluids) ሰጥተውኛል ሳላውቀው በዛው ሄድኩ። ኦፕሬት ሲያደርጉ ያ ክፉ መንፈስ ይታገል ነበር። ብዙ ግዜ ስለፈጀባቸው እነሱም ገርሟቸዋል። ሰርጀሪ እያደረጉ እያለ ጥቂት እንደቆዩ ደም በግራ ሳንባዬ ላይ ሲፈስ ያ የልብ ትርታዬን የሚያሳየው መሳሪያ ትክክል አልነበረም። ልጆቼን ጠርተው “እንደገና ሰርጀሪ መደረግ አለባትና ፈርሙልን” አሏቸው። አሁን በዚህ አካባቢ /የግራ ጎኗን እያሳየች/ ሰርጀሪ አድርገው ደሙን ለመምጠጥ ቢሞክሩም አልተቻለም። እንደገና ሌላ ሰርጀሪ ያስፈልጋታል ተባለ ለሶስተኛ ግዜ። አሁንም በጀርባዬ አደረጉ ቱቦ በሳንባዬ ላይ ቀብረው ደሙን እየመጠጠ እንዲያወጣ አደረጉ። ከጎን ምን ያህል ደም እንደወጣ የሚነግራቸው መሳሪያ አለ። ሳንባዬ ስር ድረስ ቱቦው አለመድረሱን ነገራቸው። ደሜ መመጠጡ አቆመ። ተጨማሪ ሌላ ባስቸኳይ ሰርጀሪ መሆን አለባት ተባለ ። የእግዚአብሄር ስም ይባረክ! ከኔ ጋር ነበር ጌታ፤ ከዚያም ረዘም ያለ ቱቦ እንጨምራለን ተባለ። የአኒስቴዥያው ብዛት አልገደለኝም። ለምን? ጌታ አብሮኝ ስላለ። ምስኪን ባርያውን ስላልጣለ ሃሌሉያ ! አመሰግነዋለሁ!
ወደ ገጽ 9 ዞሯል
ገ ጽ8
ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ
ዶ/ር ምሕረት ገ/ፃዲቅ
ጥቂት ቅንጭብጫቢ ታሪክ ቀመስ ትዝብቶችን ስተርክ ታገሱኝ። ፍሰትና ዝምድና ያላቸው ባይመስል አትሰልቹኝ። አውሮፕላን ከማኮብኮቢያው እንጂ በማኮብኮቢያው ላይ እንደማይበር እንዲሁም ለእኔም ወደ ርዕሰ ጉዳዬ መንደርደሪያዎቼ ናቸው። እዚህ ደህና ካኮበኮብን በሃተታው ሳላሰለቻችሁ ሃሳቤን አጠር ጠብሰቅ አድርጌ በቶሎ እቋጫለሁ። የዛሬ ሃያ አመት ገደማ የመጀመሪያ አመት ኮሌጅ ተማሪ ሳለሁ የተነሳሁትን ፎቶ ካዛሬው እኔ ጋር ሳስተያየው ያለው ልዩነት ብዙ ነው። ከሁሉ ጎልቶ የሚታየው ግን ከስተፊት የራስቅሌ ሸሽቶ ከአገጭ ከጉንጬ የሰፈረው ጸጉሬ ነው። ይህ ከቁጥጥሬም ከፈቃዴም ዉጪ የሆነ ለውጥ ነው። ዝግመታዊ ተፈጥሮአዊ ለውጥ። ያሳለፍናቸው 6 ወራት በሰሜን አፍሪካና መካከለኛው ምስራቅ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ማዕበል እንደሰደድ እሳት የተቀጣጠለበት ጊዜ ነው። በአልጄርያና ቱኒዚያ የጀመረው ነውጥ ግብጽና ሊቢያን አመሳቅሎ ሶርያና የመንንም እየናጠ ይገኛል። በዙርያ ገባው ያሉ ሌሎቹም ሃገሮች ነውጡን ከተቻለ ለማፈን ካልሆነም ለማስተንፈስ ሽቅብ ቁልቁል እያሉ ነው።
መልሕቅ
አገር ያስደገደጉ ፤ ሃያና ሰላሳ አመት ዙፋን ላይ ተቆናጠው የከረሙ መሪዎች አንድም ለስደት ተዳርገው አልያም ዘብጥያ ወርደው ማየቱ የምድር መንቀጥቀጥ ባህሩን ሲሞግደው ከሚፈጠረው ሱናሚ የሕዝብ ቁጣ እጅግም ያልተለየ እንደሆን ያሳያል። ንዝረታዊ ህዝብ ወለድ ለውጥ። ድሮ ድሮ እንደዛሬ መዋዕለ ህጻናት አገሩን ሳይሞሉት የቄስ ተማሪ ቤቶች ነበሩ፤ እኛንም አገርንም ያቀኑ። እኛ ሰፈርም የታወቁ የኔታ ዘነበ የተሰኙ ደብተራ መምህር ነበሩን። በዛን ጊዜ በታላቁ ተማሪ ቤት ያገሩን ልጅ ሁሉ ከ”ሀሁ” እስከ “አቡጊዳ” ብሎም “ዳዊት” እንድንደግም ያበቁን እሳቸው ናቸው። ሂሳብም ቢሆን በሳችው እጅ የተማረ ከቁጥር ጀምሮ አራቱን መደቦች አጠናቆ ነው ባርኮታቸውን የሚቀበል። ታድያ የተማርንበት ትምህርት ቤትም ትልቅ የቆርቆሮ መጋዘን ሲሆን ... በወቅቱ (በልጅነት አይኔ) ለሰማይ የቀረበ ከፍታ ያለውና ከባህር የሰፋ ህንጻ ሆኖ ነበር የሚታየኝ። ትልቁ ደስታችን ደግሞ ከትምህርት በኋላ ደውል ሲደወል የኔታን አጅቦ ወደቤት እየተንጫጫን መሄድ ነበር። አሜሪካን አገር ቆይቼ በ 2009 እንደፈረንጆቹ... ቤተሰብ ለመጠየቅ በሄድኩ ግዜ ቄስ ተማሪቤቴንም ልጎበኝ ሄጄ ነበር። ማመን ያቃተኝ ነገር ያገኘሁት ትንሽ ደሳሳ የቆርቆሮ ቤት ሲሆን ዉስጡ የኔታም ልጆቹም የሉ። አሁን ወፍጮ ቤት ሆኖ የወፍጮ ግምግምታ እና የዱቄት ብናኝ ነው የሞላው። የተሰማኝ ስሜት ድብልቅልቅ ስለነበር ስም አላገኘሁለትም። የዛሬ 30 አመት የሞቀ የደመቀው የየኔታ ዘነበ ቄስ ትምህርት ቤት የዛሬ የሰፈር ወፍጮ ... የያኔ የቄስ ተማሪ ሆኖ ከየኔታ ዘነበ እግር ስር ድክድክ ይል የነበረ አንድ ፍሬ ህጻን ደግሞ በፈረንጅ ሃገር የአዕምሮ ሃኪም ሆኖ... ፊት ለፊት ተፋጠን ቆመናል ... እኔም ትምህርት ቤቴም ተቀይረናል። ለውጥ ቦታ ጊዜና
ማንነት የማይመርጥ ... የማይቆም የሕይወት ሂደትና መርህ። እንዳየሁት ከሆነ እዛ ስፍራ ያልተለወጠ አንድ ነገር ቢኖር ራሱ ለውጥ ብቻ ነበር። እኔም በተማሪ ቤቴ ተለውጬበት ጀርባዬን ሰጥቼው ሄድኩ... ከዛም በኋላ አልተመለስኩም ... ይሄም ለውጥ እኮ ነው። ድሮ ቢሆን ... ትምህርት ቤቴ ያደኩብሽ የተማርኩብሽ ኑሪ ለዘላለም እንደኮራሁብሽ ነበር የምል...ለዛውም በሙዚቃ። ጥንት ጥንት ትልልቆቹ ስልጣኔዎች በግሪክ፣ በግብጽ፣ በህንድ፣ በቻይና፣ በባቢሎን (ኢራቅ)ና ፋርስ (ኢራን) እንደነበሩ ታሪክና የከርሰ ምድር ምርምሮች ያስረዳሉ። የኛንም ምድር ጨምሮ በሌሎች የአፍሪካ አካባቢዎችም ታላላቅ ስልጣኔዎች እንደነበሩ የሚያሳዩ ሊካዱ የማይቻሉ መረጃዎች አሉ። የኢኮኖሚና የስልጣኔው ሚዛን ወደ ምዕራቡ ዞሮም ምዕተ አመታት አሳልፎ እንደቆየ ይታወቃል። ባለፉት ጥቂት አስርት አመታት የታየው የአለም አካሄድ እንደሚያስረዳው ግን የሃይል ሚዛኑ ወደምስራቅና ወደደቡብ እያዘነበለ ነው ይባላል። ከቻይና ህንድና ብራዚልን የመሳሰሉ አገሮች ግስጋሴ በተጨማሪ፣ የምዕራባውያኑ የሞራል ልልነትና የማህበራዊ ህይወት መሸርሸር ከጊዜ ወደ ጊዜ መባባስ ሁሉንም ያባነነ የነገሩንም አይቀሬነት ያስገነዘበ ጠቋሚ እየሆነ ነው። አፍሪካውያን የወረድንበት የታችዮሽ አዘቅትና የምዕተ አመታት እንቅልፍ አሁንም የበዪ ተመልካች እንዳያደርገን ያለውንም ስጋት መጠቆሙ ተገቢ ይመስለናል። የአለም ህዝብ ባለፈው ሃምሳ አመት ብቻ ከ3 ቢሊዮን ወደ 7 ቢሊዮን ገደማ ማደጉ፤ በትራንስፕርትና መገናኛ ዕድገት አለም አንዲት ትንሽ መንደር መሆኗ፤ የሰው ልጅ እውቀት ልቀትና የመረጃ ምጥቀት ብዛት ሁሉ ሲታይ አለም አንዳች አይቀሬ አዲስ ነገር ለመቀበል ተዘጋጅታ የምትጠብቅ ድርስ ነፍሰ ጡር ትመስላለች። ሁሉን አቀፍ ስር ነቀል ሁለንተናዊ ለውጥ!!
ወደ ገጽ 9 ዞሯል
ገ ጽ9
ማራናታ!
67 ደቂቃዎች ከዘማሪ ሒሩት ..... ከገጽ 7 የዞረ እንደገና ስለበዛባት ስጋዋን ብቻ የሚያደነዝዝ ነገር እንጂ ሙሉ አኒስቴዥያ አንሰጣትም አሉ። የሰጡኝ አኒስቴዥያ ከውጭ ...ወደ ውስጥ ሲገባ ግን አደጋና ህመም አለው። ከዚያ የላይኛውን ሲቀዱ አልተሰማኝም ። ሰንጥቀው ሲገቡና ቱቦውን ሲያስገቡ “ኢየሱስ!” ብዬ ጮኽኩ። በዚያ ሰዓት ያቺ 12 ዓመት ደም የሚፈሳት ሴት ነበረች የታየችኝ። “ጌታ ሆይ ለኔም ድረስልኝ! ይሄው ልብስህን ይዣለሁ” ብዬ ትራሱን እንቅ አድርጌ ይዤ ስጮህ ሰዓቱ አጠረልኝ። 45 ደቂቃ ብቻ ሆነ። ቱቦው ተጨመረ አሻሸጉትና ከሰርጀሪው አልጋ ላይ ወደ ኖርማሉ አልጋ ላይ አደረጉኝና ወደ መኝታ ክፍሏ ትሂድ አሉኝ። የሚገርመው ነገር ሰባት ግዜ ነው ሰርጀሪ ያደረጉኝ። ስምንተኛዋን እንኳን ባንቆጥራት የቀረ ቱቦውን ለማውጣት ብቻ ነውና። ጠጠሩን ያወጡት በመጨረሻው በ7ኛው ሰርጀሪ ግዜ ነበር። ከዚያ በኋላ መኝታ ቤቴ ተኛሁ። ጌታ ከዚህ ጉድ
አወጣኝ። ልጆቼም የሞትኩ መስሏቸው እጅግ አዝነው ነበር። ራራላቸው። እኔም ተመልሼ ዛሬ በፊቱ ቆሜ ላገለግል በቃሁ። እንኳን ሰባቴ በኔ አቅም ሁለቴ እንኳን የምችል አልነበርኩም። ታዲያስ የሱን ክንድ አየሁት! ታላቅ ስራ ነው የሰራው። መልሕቅ፦ ከአለማዊ ሙዚቃ ድምፃዊነት ወደ መንፈሳዊ ዘማሪነት ለመሸጋገር የከበደሽ ነገር ነበር? ሒሩት፦ ሒሩት እግዚአብሄር ይመስገን! እኔ ወደ ጌታ ቤት ከመምጣቴ በፊት “እንዲህ አይነትስ ነገር ቢመጣ? እንዲህና እንዲያስ ቢሆን?” እያልኩ እጠይቀው ነበር አለሙን። “እሱን እግዚአብሄር ይረከበዋል አንቺ አይደለሽም” ነበር መልሱ ። ስለዚህም ድፍረት በውስጤ ተሞላ። አገልጋዮቹ ራሳቸው ይዘውኝ እየሄዱ ቅድም እንደተናገርኩት እንዳገለግል ያደርጋሉ። ሌላው ከዚህ ሁሉ በፊት አለማዊ እያለሁ የብስራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያን እናዳምጥ ነበር።
ብዙ መዝሙሮችን አናውቅም፣ ቤ/ክ አንሄድም ግን የብስራተ ወንጌል ሬዲዮ ጣቢያን እየሰማን... በዚያ ዘመን ይዘመር የነበረውን “ ማረኝ አቤቱ ፈጣሪዬ እኔም አውቃለሁ በደሌን”የሚለውን መዝሙር መዘመራችንን አስታውሳለሁ። እሱ በኛ ቤት ትልቅ መዝሙር ነበር አሁንም ነው። እናቴ ልጆቿንና የኔን ልጆች ትሰበስብና በኔ አውራጅነት “ ማረኝ አቤቱ ....” እያልን እንዘምር ነበር። መዝሙሮችን እያዳመጥንና እየዘመርን እየበረታን መሄዳችን በጌታ ቤት ከባዶ እንዳንጀምር ረድቶኛል ። መዝሙሩ ለኛ አዲስ አይደለም ማለቴ ነው። ጌታን እኔና እናቴ አንድ ቀን ነው የተቀበልነው። ወዲያው ብድግ ብለን ስንዘምር ይገርማቸው ነበር። ጌታ በዚህ ዓይነት ስለሆነ ያሸጋገረን ከዚያ ወደዚህኛው ስመጣ ብዙ አልከበደኝም። እርሱ ሁሉን ነገር አዘጋጀ ማለት ነው። ያ የብስራተ ወንጌል ልምምዴ በጣም ረዳኝ።
ወደ ገጽ 11 ዞሯል
ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ ከገጽ 8 የዞረ ለውጥ ሸሽተን የምናመልጠው፣ ጠልተን የምናስቀረው፣ ገፍተን የምንጥለው ነገር አለመሆኑን ከላይ ያየናችው ነጥቦች ጥሩ መረጃዎች ናቸው። በግል በቤተሰብ፣ በህብረተሰብ በሃገር ፣ በትውልድና በአለም ደረጃ ለውጥ ሁሌ አለ። ለውጥ አመቱን ሙሉ ሲፈስ ከርሞ በክረምት ያገኘውን ጠራርጎ እንደሚሄድ የወንዝ ደራሽ ጎርፍ ሁሌም ያለ ድንገትም የሚመጣ የህይወት ህግ ነው። ታድያ ለውጥ አይቀሬ ከሆነ ምርጫነቱ ምን ላይ ነው? በለውጥ ላይ ምን ለውጥ ማምጣት እንችላለን? ካልቻልንስ ስለለውጥ አወራን አላወራን ምን ‘ለውጥ ‘ ያመጣል?? የለውጥ ሐዋርያ እያልንስ የምናደንቃቸውና እንደ አርአያ የምናያቸው ምን ስላደረጉና ስለሆኑ ነው? ይህን እና የመሳሰሉ ጥያቄዎች ተገቢ ብቻ ሳይሆኑ በበቂ መመለሳቸው የዚህን ጽሁፍ ስኬት ይለካዋል።
ይህንንም በሚቀጥሉት ንዑስ ሃሳቦች ለመዳሰስ እንሞክራለን። የለውጥ ትርጉምና አንዳንድ ጠቃሚ መርሆዎች፡ ቢያንስ ለዚህ ጽሁፍ መገልገያና ድንበር ማበጂያ ብሎም ማመሳከሪያ ይሆነን ዘንድ ለውጥ ስንል ምን ማለታችን እንደሆነ ባጭሩም ቢሆን ትርጉም መስጠቱ ተገቢ ነው። ለውጥ በመሰረቱ ነገሮች ባሉበት ሁኔታና ደረጃ ከመቆየት ይልቅ ወደተለየ፣ ወደ አዲስ መልክና ደረጃ የመቀየራቸው ሂደት ብሎም ውጤት ነው። ይህ አጠቃላይ ሃሳቡ ሲሆን የዚህ ጽሁፍ አትኩሮት ግን የአንድ ሁኔታ፣ ግለሰብ፣ ቤተሰብ፣ ህብረተሰብ፣ ሃገር ወደተፈላጊ፤ ጠቃሚና የላቀ ደረጃ ለመድረስ በጊዜ ውስጥ የሚደረግን የሽግግር ጉዞና የፍጻሜ መዳረሻ ማለታችን ነው። በታወቀው የተደላደለ የትናንት ወደብ የቆመ የዛሬን መርከብ መልሕቅ ሰብስቦ ወዳልታወቀው የነገ ሩቅ ግዛት በአደገኛ የዕድል ባህር ላይ የሚደረግ የድፍረትና የእምነት ቀዘፋ ነው። የትናንትን ትዝታና የዛሬን ምቾት እምቢ ብሎ ለነገ ጥሪ የሚሰጥ ምላሽ ነው።
እውነተኛና ትክክለኛ ለውጥ በዘፈቀደና በእድል ሳይሆን የራሱን መርህ ተከትሎ የሚገኝ ነው። 1. እውነተኛ ለውጥ ከራስ መጀመር አለበት ፤ ስኬታማ የሚባለው ግን ወደሌሎች በሚያዛምተው በጎ ተጽእኖና አስተዋጽዖ ተለክቶ ነው፡ 2. ለውጥ ከዉስጥ ከአስተሳሰብና ከማንነታችን መጀመር አለበት። በባህርይና በአኗኗር ካልታየ ግን ፍሬ ቢስ መና ነው። 3. ለውጥ በጊዜ ዉስጥ ብቻ ስለሚሆን ትዕግስትና ጽናትን ይጠይቃል፤ የሚያመልጥ ዕድል ሊሆን ስለሚችልም ድፍረትና ቆራጥ ዉሳኔን ይጠይቃል። 4. ያለ መስዋዕትነት የሚመጣ ለውጥ የለም። ታላቅ ለውጥ ታላቅ ዋጋ ያስከፍላል - ህይወት የሚቀይሩ ለውጦች ዋጋቸውም የህይወት መስዋዕትነት ሳይሆን አይቀርም። ወደ ገጽ 11 ዞሯል
ገ ጽ10
ብፅዕት ድንግል ማርያም በሰማይ የሚበሩትን አዕዋፍት፥ በምድር የሚንቀሳቀሱትን እንስሳት፥ በባህር ሆድ ውስጥ የሚርመሰመሱትን ፍጥረታትንና በአጠቃላይ በዚህ ሰለሞን ለማ በግዙፉ ዓለማት የምናያቸውንና የማናያቸውን ስነ-ፍጥረታት በሙሉ እግዚአብሔር በአፉ ቃል “ይሁን”በማለት ዕውን አደረጋቸው። (ዘፍ1:24-25) ይህንን የሰው ልጅ አዕምሮ ሊረዳውና አንደበት ሊገልፀው በማይችለው አስደናቂ ሁኔታ የፈጠረውን እያንዳንዱን ፍጥረት ድንበርም አበጀለት። በመጨረሻም እጅግ ክቡርና የፍጥረቱ ሁሉ ቁንጮ (The crown of His creaon) የሆነውን ሰውን ግን ከአፈር አበጃጅቶ መለኮታዊ እስትንፋሱን እፍ በማለት ህያው ነፍስ ዘርቶበት የመለኮታዊ ባህርይው ተካፋይ እንዲሆን አደረገው። ፈቃድና ምርጫን ቸረው። የማሰብና የማስተዋልን ኅሊና አጎናፀፈው ። ይህ ብቻ አይደለም ይህን የተፈጠረውን ፍጥረት “ሁሉ” ሊያስተዳድር የሚችልበትን ዕውቀት፣ ጥበብንና ስልጣንን ከአደራ ጭምር በመስጠት በኤደን ገነት እንዳኖረው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። እግዚአብሔር ከአዳም ከጎኑ አጥንት ወስዶ አመቺ የምትሆነውንና የምትረዳውን ሴት ሔዋንን አበጃጅቶ ወደ አዳም በማምጣት “ብዙ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት፥ ግዙአትም የባህርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ግዙአቸው (ዘፍ 1፡28) ” በማለት ባረካቸው። ለእነርሱም ደግሞ ገዢና ፈጣሪ ጌታ እንዳላቸው እንዳይዘነጉ “ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ። ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና” (ዘፍ 2፡17) ብሎ አስጠነቀቃቸው። ይሁንና በሔዋን ተላላነት የፈጣሪያቸውን ቅዱስ ሕግ ተላልፈው ተገኙ። ይህንን የዛፍ ፍሬ ስለበሉ ሳይሆን የእግዚአብሔርን ቅዱስ አደራ መጠበቅና መታዘዝ ስለተሳናቸው የእግዚአብሔር የሞት ፍርድ ብያኔ ሊያገኛቸው ግድ ሆነ። እግዚአብሔር ይህንን ፍሬ እንዳይበሉ ሲነግራቸው በፍሬው ውስጥ መርዝን ወይም ሞትን አስቀምጦ አልነበረም። ነገር ግን ልካቸውንና ድንበራቸውን አውቀው በተፈቀደላቸውና ባልተፈቀደላቸው ጉዳይ ላይ እውቅና በመስጠት በትህትና፣ በሰላምና በእረፍት እንዲኖሩ ነበር እንጂ።
መልሕቅ
እንደ እውነቱ ከሆነ፣ አሳቹ ሰይጣን እንዳለው እግዚአብሔር መለኮታዊ እውቀቱን ከአፈር አበጅቶ ለሰራው ሰው ለመደበቅ ወይም ለመሸሽግ ፈልጎ አልነበረም። ይልቁንም ፍጥረት የእግዚአብሔርን ጥበብ፣ እውቀት፣ አምላክነት ወይም መለኮትነትን ለመረዳት ጨርሶ ነገር ስለማይቻለው እንጂ። ሰው ካለመኖር ወደ መኖር የመጣ ፍጥረት ነው። ስለሆነም ለዘለዓለም የኖረውንና የሚኖረውን የፈጣሪውን ጥበብ፣ ኃይልም ሆነ ሙሉ ዕውቀት ሊረዳውም ሆነ ሊኖረው አይችልም። እግዚአብሔር አምላክ ብቻ በአንድ ጊዜ በሁሉም ስፍራ የመኖርም ሆነ የመገኘት ችሎታ አለው። ሁሉንም ነገር በዝርዝር የማወቅ ብቃት አለው። በአንድ ጊዜ ከቁጥር የበዙ ነገሮችን በተጓዳኝ ማድረግና ማከናወን መጀመርና ማጠናቀቅ የሚችል ፈጣሪ ነው። ሰይጣን በእባብ መልክ ተመስሎ ለአዳምና ለሔዋን የነገራቸውን እውነት የሚመስለውን ሐሰት አምነው በመቀበላቸው ፈጣሪያቸውን ዋሾ (ዘፍ 3፡45) ሰይጣንን ግን እንደ ሚስጥር አዋቂ አድርገው በመቀበል ሹክ ያላቸውን በማመናቸው ሞት የተባለው የማይለመድ እንግዳ ወደ ፍጥረተ ዓለም በነዚህ ሰዎች ምክንያት መሰስ ብሎ ገባ። የፈጣሪያቸውን ሕግ የተላለፉትን አዳምንና ሔዋንን ብቻ ሳይሆን ከአብራካቸው ሊመጣ ያለውን የሰውን ዘር ሁሉ ከዚህ ዘለዓለማዊ የሞት ፍርድ ለማዳን እግዚአብሔር የምኅረት ቃል ኪዳን ለአዳምና ለሔዋን ገባላቸው። የሥነ መለኮት ሊቃውንት “የመጀመርያው ወንጌል”ወይም “የመጀመርያው የምሥራች”ብለው የሰየሙትን የደህንነትን የተስፋ ኪዳን በሴቷ ዘር አማካኝነት እንደሚመጣና፤ ይህም የሚመጣው ዘር ያሳታቸውንና ለሞት ፍርድ እንዲዳረጉ ያደረጋቸውን ፍጥረት ራሱን እንደሚቀጠቅጠው እግዚአብሔር አምላክ በዚያው በኤደን ገነት ውስጥ ተናገረ። (ዘፍ 3፡15) ከዚህም እርግጠኛና አምላካዊ ኪዳን የተነሳ ብዙ እስራኤላዊያን ሴቶች ወንድ ልጅ በወለዱ ጊዜ ይህ የተባለለት “አዳኝ” ይሆንን በሚል ተስፋ ውስጥ ይዋትቱ እንደነበር የመጽሐፍ ቅዱስ አዋቂዎች ይናገራሉ። በተለያየ ወቅት እስራኤላዊያን እግዚአብሔርን በድለው በተገኙበት ወቅት፣ ለግዞትና ለጭቆና ለሌሎች እስራኤላዊያን ላልሆኑና ለሚጠሏዋቸው አሳልፎ ይሰጣቸው ነበር። ከዚያም ሕዝበ እስራኤል በእግዚአብሔር ፊት ራሱን አዋርዶ፣ አልቅሶ፣ ማቅ ለብሶ
ምህረትን ካገኘ በኋላ ኃያልና ብርቱ ሰው ከመካከላቸው አስነስቶ በአምላካቸው ረዳትነትና በዚህ ሰውም መሪነት ነፃነታቸውን ያስመልሱ ነበር። እንደዚህ ባለ የመውደቅና የመነሳት ዑደት (ሽክርክሪት) ለተወሰኑ መቶ ዓመታት ባሳለፉበት ዘመን ሊመጣ ያለውን የመሲሁን ሕዝብን ከኃጢአትና ከዘላለም ሞት ፍጹም ነፃ የማውጣትን አገልግሎት ለማመልከት እንደጥላ በመሆን አሻራቸውን ትተው አለፉ እንጂ እነርሱ ግን መሲሁ አልነበሩም። ለመንደርደሪያነት ይህን ያህል ካልኩ ወደ ርዕሰ ነገሩ ላቅና። እስራኤላዊያን ይህን የተነገረለትን “የሴቷ ዘር” የተባለውን “መሲህ” ወይም “አዳኝ” እንደሚመጣና እንደሚታደጋቸው ለዘመናት ሲጠባበቁ ነው የኖሩት። እግዚአብሔር ስለዚህ የሰው ልጆች ታዳጊ ስለሆነው ጌታችን በኤደን ገነት ከተናገረ ከሺህ ዓመታት በኋላና ከመወለዱም ሰባት መቶ _አመታት ያህል ቀደም ብሎ አንድ ታላቅ ነቢይ በእስራኤል ምድር ላይ አስገራሚ ትንቢትን ተናገረ። ይህ ነቢይ “ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፣ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች” (ኢሳያስ 7፡14) በማለት የዚህን ወንድ ልጅ ባልተለመደ ሁኔታ ከድንግል መወለድ አበሰረ። ከተወለደና ካደገ በኋላም የሚደርስበትን ስቃይ፣ ግርፋት፣ መከራና ግፍ ገለፀ። በዚህ አላበቃም ይህ የሕማም ሰው፣ ደዌንም የሚያውቅ፣ የሰው በደል የሚያደቅቀው እንደሆነና “ቁስለኛው ፈዋሽ” (The Wounded Healer) ብሎ አንድ የዘመናችን ሰው እንደጻፈለት በዚህ ሰው ቁስል ፈውስ እንዳለም ጭምር አመለከተ። እግዚአብሔር እንዲህ ያለ አስደናቂና ሊታመኑ አዳጋች የሆኑትን ተአምራትና ድንቅን እጅግ ብዙ ጊዜ አድርጓል። አሁንም እንደፈቃዱ እያደረገና እየሰራ አለ። ይኖራልም። እግዚአብሔር በመለኮታዊ ጥበቡና ኃይሉ ካደረጋቸውና በመጽሐፍ ቅዱስም ውስጥ ተመዝግበውልን ካሉት መካከል በአይነቱ ብቸኛ በክስተቱም ያልተደገመ ነገር ቢኖር የዚህች ወንድ የማታውቀዋ የድንግል ሴት ወንድ ልጅን መውለድ ነው። ለዚህ ታላቅ በዓይነቱ የመጀመርያም የመጨረሻም ለሆነው ነገር እግዚአብሔር የተጠቀመው የአንድ በናዝሬት ከተማ ተወልዳ ያደገች አይሁዳዊት ሴት ልጅን ነበር። ይህች ሴት ልጅ በወቅቱ በነበረው ወግ፣ ባህል፣ በአይሁድ እምነት በትህትናና በጨዋነት ለማደጓ ይህን አይሁድ ሁሉ ይጠብቀው የነበረውን፤ እግዚአብሔር በኤደን ገነት ከሺህ ዓመታት በፊት ለሰው ዘር ሁሉ ከዘለዓለም ሞት መትረፊያ የሆነውን “ዘር” እንደምትሸከም “የምስራች” እንዲላት ተልኮ ከነበረው ከእግዚአብሔር መልዕክተኛ ወደ ገጽ 13 ዞሯል
ገ ጽ11
ማራናታ!
ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ ከገጽ 9 የዞረ 5. ለውጥ እውነትን በመፈለግ ተጀምሮ እውነትን በመታዘዝ የሚደመደም ምናኔ ነው። ደግሞ ደጋግሞ የሚደረግ ማብቂያ የሌለው። ይሉኝታ፤ የሰዎች አስተያየትና ተቃውሞ፤ ስህተትና ወድቀት እንዲሁም አቋራጭ አማራጮች የለውጥ አጨናጋፊ መስናክሎች ናቸው። እውነተኛ ለውጥ ከእውነት ሌላ ምን ፍሬ ሊኖረው ይችላል? 6. ለውጥ የብቸኝነት ጉዞ ቢሆንም የግል ንብረት ወይም የእውቅና መሰላል አይደለም። ስለሌሎች ከሌሎች ጋር የሚደረግ ጥልፍልፍ ግንኙነት ነው። 7. ለውጥ ተቃዋሚው ብዙ ብቻ ሳይሆን ካልተጠበቀም አቅጣጫ ሊመጣ ይችላል። ለውጥ የተለወጡ እንጂ ያልተለወጡ
ወዳጆች የሉትም። ብዙ መለወጥ የሚገባቸው ሰዎች የለውጥ ዋነኛ ጠላቶቹ ይሆናሉ።
የለውጥ አይነቶች፡ ለውጥ ተመልካቾች፤ ተቃዋሚዎች፣ ፈርቀዳጆች ፣ ባይተዋሮችና ተጎጂዎችን ማፍራቱ አይቀርም። ይህም በዕድል ወይም የአጋጣሚ ዉጤት ሳይሆን የሰዎች ፈቃደኝነት፣ ዝግጅት፣ መሰጠትና እውቀት የሚወስነው ጉዳይ ነው። ለውጥ ከግል እስከ ቤተሰብ፣ ከአካባቢ እስከ ሃገር አልፎም ተርፎ ትውልድንና የአለምን ሰፊ ክፍል የሚዳስስና የሚያካልል ሊሆን ይችላል።
የለውጥን አጠቃላይ አካሄድና ባህርይ ስንመለከት ዋና ዋና አይነት የለውጥ አይነቶች እንዳሉ ማጤን ይቻላል። በአብዛኛው በህብረተሰባዊ ለውጦች ላይ ጎልተው ቢታዩም በግልና በቤተስብ ደረጃም የሚታየው ለውጥ ባትኩሮት ካየነው በመሰረታዊ ይዘቱ የተለየ አይደለም። ለውጥ አብዮታዊ (revolutionary ተኃድሷዊ (reformation) ዝግመታዊ (evolutionary) ንጥቀታዊ (transformational) ወይም ህዳሴያዊ (renaissance) ሊሆን ይችላል።
ወደ ገጽ 12 ዞሯል
67 ደቂቃዎች ከዘማሪ ሒሩት ከገጽ 9 የዞረ አለሙ ደግሞ እየመጣ ምን ማድረግ እንዳለብን ያስተምረናል። ለሎች ወገኖች ይዞ እየመጣ ቤት ውስጥ ይፀለይልናል። በቃ ውስጤ በጌታ እንዲያድግ ያደረገው እሱ ነው። እግዚአብሄር ይመስገን! ለዚህ ሰው ግን እንድትፀልዩለት እለምናችኋለሁ። አሁን እሱ ከጌታ ቤት ወጥቷል። በጣም ያሳዝነኛል ሳስበው። ወንድሜንም እግዚአብሄር ያስበው ወደራሱ እንዲመለስ ..../ቆዘመች/ መልሕቅ፦ መልሕቅ ባሁን ሰዓት ያለሽ አገልግሎት ምን ይመስላል? ባገልግሎት ላይ ያጋጠመሽ ነገር ካለ? ሒሩት፦ እግዚአብሄር ይመስገን ጌታ ያዘጋጀልኝ ብዙ ነገር አለ። በየክፍለሀገሩ በሙሉ ዞሬያለሁኝ ። አንድ ግዜ ናዝሬት ላይ ሳገለግል ሴትየዋ ፊት ለፊት ታየኛለች እኔም አያታለሁ ። ለምን እንደማያትም አላወቅኩም። ወደኋላዋ በጀርባዋ ወደቀች። ብቻ ያ ክፉ መንፈስ ከላይዋ ላይ ሲወጣ አየሁና “ጌታ በመዝሙርም ትሰራለህ?” አልኩ። ደግሞ ሌላ አገር ሄጄ ስታዲየም ውስጥ ከፈረንጆች ጋር ስናገለግል ሴትየዋን በጋሪ አመጧት። አብጣ አብጣ ይሄን አክላለች። /በእጇ እያሳየች / አራት ሰው ይዟት መጥቶ ሳሩ ላይ አንጥፈውላት ተኝታ አይኗን አፍጣ የሚደረገውን ነገር ሁሉ ታያለች። ግዜው ስለረዘመ መዝሙሩን አላስታውሰውም እየዘመርኩ ነበር። ስዘምር እንደዚህ ዓይነት ነገር ማየት እወዳለሁ ምን እንደሆን አላውቅም። አያታለሁ እሷም ወደላይ ቀና ብላ ታያለች። ከዚያ በኋላ
እየዘመርኩ እያየኋት ፣ ስልቻ ነገር ሲራገፍ ሙሽሽ ይል የለም? ያ እንደዛ አብጦ የነበረው ገላዋ ኡፍፍፍፍ ብሎ ወደ ውስጥ ስምጥ አለ ። ከመቅጽበት ብድግ አትልም! ከተኛችበት። ሙዚቃው ይጫወታል እኔ ረስቼ እሷን ነው የማየው። ሮጣ መጣች መድረክ ላይ ። ነጮች በጣልቃ እንዲህ የሚገባባቸው አይፈልጉም። አስተናጋጆቹ “ ምንድነው?...በኋላ ትመሰክሪያለሽ” ቢሏት “ፍጹም ትዕግስት የለኝም አሁኑኑ መመስከር አለብኝ” አለች። “ኧረ እባክሽን” ብትባል “የፈለገው ነገር ይሁን ጌታ ያደረገልኝን አሁኑኑ መናገር አለብኝ “ አለች። ለካስ ሕዝቡ ሁሉ በሽተኛ መሆኗን ያውቃል። 10 ደቂቃ ስጧት ተባለ። አልቻለችም መቀመጥ ከደስታዋ የተነሳ። ከዚያ በኋላ ዕድሉ ተሰጣት። “ሒሩት በቀለ ስትዘምር አያት ነበር እሷም ታየኝ ነበር ..እንዲህ ከሆዴ ውስጥ ብድግ ብሎ በራሴ ውስጥ እንደ ጭስ ሲወጣ ተሰማኝ ... እንዴት ልታገስ ታዲያ? መመስከር አለብኝ” አለች ። ያ ሁሉ ሰው ተላቀሰ ። አላየናትም አንል አይተናል.... ይሄንን ድንቅ አይቻለሁ። ሌላው ደግሞ ከጅማ አልፎ ቴፒ የሚባል ሩቅ ሀገር ለአገልግሎት ሄደናል ። ሀይለኛ ፀሐይ ስለነበር ከመድረኩ ጀርባ ነው ያለሁት። አንድ ከሌላ አካባቢ የመጣች ሴትዮ ልጇን ታቅፋ መጣች ። ወደዚያ መሄድም ከሰውም ጋር መደባለቅ ያልፈለገች ግራ የገባት ሴት ናት። ልጇን ታቅፋ ቆማለች። ሕጻኗ የ4 አመት ልጅ የምትሆን ይመስለኛል። “ ነይ እስቲ ...ምን ሆነሻል?” አልኳት። “እባክሽን ልጄ አትሄድም አትናገርም ...አንዴ ቁጭ ካለችም አትነሳም ....አትድንም ” አለችኝ። እስቲ ነይ እዚህ መኪናጋ እንሂድ አልኳት የማን መኪና እንደሆን እንኳን አላውቅም።
እዚያ ጥግ ቆምንና “እስቲ ቱታዋን ወደታች ዝቅ አድርጊው” አልኳትና ሁልግዜ ፀልዬ የምይዛትን ብልቃጥ አውጥቼ ዘይቴን ቀባኋት። አፏን ሁሉ ቀባኋትና “ እስቲ ልቀቂያት” አልኳት። የሚገርም ነው ስትለቀቅ ድንኩር ድንኩር አትልም መሰላችሁ! ልጇን ይዛት ልትመሰክር መድረክ ላይ ወጣች። ይህንን የእግዚአብሔር ተዓምር ያዩ ሰዎች ምግብ የምንበላበት ቦታ ላይ እያለን አንዷ ጨርቄን ጎተት አደረገችና “አንዱ አይኔ አያይም” አለችኝ።፡ እኔ ምን ላድርግ ታዲያ? እደነግጣለሁ እንደዚህ ዓይነት ጥያቄ ስሠማ። “እኔ አላውቅም ጌታዬ ያንተን ስም ብቻ እየጠራሁ እፀልያለሁ” ብዬ ያቺ የፈረደባት ቅባት አለች፤ እሷን አውጥቼ ስቀባት አይኗ ብርት አይልም! ኡ! ጌታ ሆይ ስምህ ይባረክ! በጣም ደስ አለኝ። አንድ ሶስት ሴቶች አይናቸው ተፈወሰ። ይህንንና ሌላም ሌላም አድርጓል። ብንናገረው ብዙ ግዜ ይፈጃል እንጂ ...። ቅድም እንደተናገርኩት ጌታ ሰው አይንቅም። ዋናው ምዕራፉ ይሄ ነው። አይንቅም። የእርሱ እኮ እስትንፋስ ቁራጮች ነን እኛ። ‘እፍ“ አለበት አይደለም የተባለው አዳምን። በቃ የእርሱ እስትንፋስ ነን እኛ። ስለዚህ እግዚአብሄር ይሄንን ሰራ። ስሙ ይባረክ!
ወደ 16ኛው ገጽ ዞሯል
ገ ጽ12
ብፅዕት ድንግል ማርያም
ታማኝ ልባም መጋቢ ማነው? ሉቃስ 12፡42
ፓስተር ጳውሎስ ጉልላት
“.....ጉዳዮ ምን ያህል ዘመን በዚህ ምድር ላይ እንደኖርን አይደለም፤ …የተሰጠህን ዘመን ምን አደረክበት? ለሚለው ጥያቄ በማያጠራጥር፣ በማያወላዳ መንገድ መልስ መስጠት መቻል አለብህ…..”
የዕድሜ ከመልአኩ ገብርኤል ጋር ያደረገችው ክልል ውስጥ እንደሆነች ይገምታሉ። ቃለ ምልልስ ያመልክታል። መልአኩ ይህን የመሰለ ሰላምታና ይህች ፈሪሃ እግዚአብሔር ያደረባት፣ አምላኳን አክባሪ ሽቁጥቁጥ፤ በዘመኑና የምሥራች እንዲህ ባለ ቋንቋና አነጋገር ሲያበስራት አንባቢ ሊገምት ብቻ በባሕሉ ከነበሩት ሴቶች ልጆች ሳይሆን በውል ሊያውቀውና ሊገነዘበው ለወላጆቿና ለነገዷ ኩራት፣ የሚገባው ነገር ቢኖር ማርያም ለእግዚአብሔርም ደግሞ ክብር ከአምላኳ ከእግዚአብሔር ጋር መልካም ሊያመጣ ባለው ከማንነቷ ጋር ግንኙነት የነበራት ሴት መሆኗን ነው። በተያያዘው ጉዳይዋ ላይ ጥንቁቅ እንደነበረች የእግዚአብሔር ቃል የሆነው “ደስ ይበልሽ” ሲላት ስለ መንፈሳዊ ደስታ፤ “ጸጋን የሞላብሽ” በማለት መጽሐፍ ቅዱስ ይመሰክርላታል። ሰላምታ ሲሰጣት ስለጸጋ፤ “ጌታ ከአንቺ መልዓኩ “ደስ ይበልሽ፣ ጸጋ የሞላብሽ ጋር ነው” “በማለት ሲያረጋግጥላትና ሆይ፣ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል ለአንድ መለኮታዊ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት።”(ሉቃስ 1፡28) አንድ ሰው ከሰው ዓላማ መመረጧን ሲነገራት በእርግጥም መካከል የተባረከ ለመሆኑ መልአክ ማርያም ለየት ላለው ጥሪ፣ ላቅ ላለው አይደለም ስጋና ደም የለበሰ ሰው እንኳ አገልግሎትና ለተቀደሰው ሲመሰክርለት ብዙ ሊኩራራና ሊኮፈስ የእግዚአብሔር ዘለዓለማዊ ሀሳብ ይችላል። የመጽሐፍ ቅዱስ የታሪክና የክብሩ መገለጫ ሆና የመመረጧ የባሕል አዋቂዎች እንደሚናገሩት ምክንያት ከአምላኳ ጋር ካላት መልካም ድንግል ማርያም ይህን የምሥራች ህብረት አኳያ እንደሆነ ያረጋግጣል ። ከመልአኩ ስትሰማ ገና የለጋ ወጣት መልዕክቱ ያልተጠባበቀችው በመሆኑ እንደሚያስደነግጣት የታወቀ ቢሆንም
ፈጣሪዋን በውል የምታውቅ፣ የብሉይ ኪዳንን ትንቢታዊ ቃል ስለመሲሁ መምጣት የተነገረውን ትጠባበቅ የነበረች ለመሆኗ የመልአኩ ገብርኤልን ሰላምታ ላጤነ እንደአስረጅነት መውሰድ ይቻላል። በዚህ አጭር ጽሑፍ ውስጥ መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ጌታችን እናት ስለ ማርያም የሚለውን ጥቂት ነገር ለመመልከት እንሞክር። ማርያም በልጅነቷ ዮሴፍ ለተባለ ሰው ታጭታ የሰርጓን ቀን እየጠበቀች ሳለ የእግዚአብሔር መልዕክተኛ የሆነው መልዓኩ ገብርኤል ድንገት ተገልጦ ድምጽ አውጥቶ ስሟን ጠርቶ “ማርያም ሆይ ትጸንሻለሽ ....ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ” ወደ ገጽ 13 ዞሯል
ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ ተገቢ ሃላፊነትንና የጊዜንና የኑሮን ህግ ካከበሩ በዚህ መንገድ ይህም ከአጀማመር፤ ከአካሄድና የሚመጣው ለውጥ ከጫናና ስጋት ከገዢ ባህርይ አኳያ ካልሆነ በቀር የጸዳ ኑሮ ለመኖር ያስችላል። ሁሉም አይነት ለውጦች ይህም የቤተሰብ፤ የህብረተሰብ፡ ተወራራሽነት እንዳላችው ግልጽ የተፈጥሮና የመሳስሉ ህጎችን ነው። ለውጥ እንደ አብይ አላማ በማክበርና በመጠበቅ ብቻ ከዕድገት (developmental) ፤ የሚገኝውን ለውጥ ያሳያል። ይህን ከሽግግር (transitional) ወይም ችላ ማለትና መጣስ የሚፈጥረው ንጥቀት(transformational) አንጻር ጦስ ቀላል አይደለም። ብዙዎቹ ሊፈረጅም ይችላል። በቀጣይነት የህይወት ለውጦች በጸጥታና እየጨመረ የሚሄድ (progressive/ በዝግታ ይከናወናሉ። ትጋትና incremental)፡ እያሰለሰ የሚከሰት ትዕግስት የዚህ ለውጥ ዋና (episodic) ወይም በድንገት መሳሪያዎች ናቸው። ሰነፍና ችኩል የሚያጥለቀልቅ (emergent) ለውጥ ግን በዚህ ለውጥ ተጎጂ ነው ሊካሄድ ይችላል። ለዚህ ጽሁፍ ቢባል ማጋነን ይሆን? አላማ ለውጥን አብዮታዊአብዮት (R ተሃድሶአዊ-ዘገምተኛ-ህዳሴያዊ(Revolu evolution)፦ tion)፦ ንጥቀታዊ በሚለው ክፍፍል አኳያ አሮጌውን አሽቀንጥሮ በመጣል ላይ የተመሰረተ በቁጣ የተጫረ ማየቱ አንዳች ተግባራዊ ፋይዳ የለውጥ ሰደድ ነው። የአሮጌውን ይኖረው ይሆን? ቀንበር ከሰበረ በኋላ የተገኘው ዝግመታዊ ለውጥ (E (Evolu volutional) tional ነጻነት ዕጣ ፋንታው ሁሌም ይህ ተፈጥሯዊ ህግንና ልማዳዊ በቅጡ የታሰበበት አይደለም። ደንብን በመጠበቅ ያለውን ግልፍተኛ እና በአመጽ የተሞላ በመንከባከብ የሚጠበቀውን ለውጥ ነው። አትኩሮቱ በማድረግ የሚመጣ ለውጥ ነው። የተበላሸውን መገርሰስ እንጂ በምን ከገጽ 11 የዞረ
የክርስቶስ የፍርድ ወንበር 2 ቆሮ. 5፡10 ፓስተር ገነቱ ይግዛው “….እያንዳንዳችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት ልንቀርብ ግድ ነው፤ ….ስለሰራነው ደግና ክፉ ሥራ እንጠየቅበታለን…..”
መልሕቅ
አዲስ ነገር ሊተካ እንደሚችል አይደለም። በእትዮጵያ የዘውዱን ስርዓት አስወግዶ በፋንታው የተተካው የኮሚኒስት ስርዓት እንዲሁም ባሁኑ ጊዜ በአረብ ሃገሮች እየተካሄደ ያለው የለውጥ ማእበል የዚህ አይነት ለውጥ ነው። በቀል፣ ጥላቻና አፍራሽነት የሚታይበት ሲሆን ከግልጽ ራእይ ይልቅ መራራ ብሶት የለውጡ ምክንያትና ጉልበት ሳይሆን አይቀርም። የተበላሸውንና ያረጀውን ለማስወገድ መልካም የለውጥ አይነት ነው። ካልተጠነቀቁ ግን ከጥቅሙ ጉዳቱ ሳያመዝን ይቀራል? ወደ ገጽ 13 የዞረ
በመጽሔታችን ላይ ጠቃሚ ፅሁፎችን ለማካፈል የምትፈልጉ፤ ግጥሞች፣ መልዕክቶች ፣ አስተያየቶች ፣ ጥያቄዎች ያላችሁ እንድትጽፉልን እናበረታታችኋለን !
ገ ጽ13
ማራናታ!
ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ ከገጽ 12 የዞረ ተሃድሶ (R (Reform eformation)፡ ation) በተበላሸውና ባረጀው ነገር ቅንጣት ተስፋ የሌለው ነገር ግን ያንን ማስወገድ የመፍትሄው ዋነኛ ነገር እንዳልሆነ የተረዳ ነው። ለአዲሱ ያለው አክብሮትና ፍቅር በአሮጌውና በተበላሸው እስረኛ የሆኑትን ነጻ የማውጣት ቅናት ይፈጥራል። ዋነኛ መሳሪያው አመጽ ሳይሆን መስዋእትነት ነው። ትልቁ ግቡም ያለውን ማፍረስ ሳይሆን ሊመጣ ያለውን መኖርና ማስተማር ነው። በችሎታና ሃይል ብልጫ ላይ ሳይሆን የሰውን ዉስጣዊ ማንነትና ባህርይ በመቀየር ላይ የተመሰረተ
ለውጥ ነው። ትልልቅ ማኅበራዊና መንፈሳዊ ተሃድሶዎች ይህንን የለውጥ ፈለግ የተከተሉ ናችው። የአብዮት አትኩሮት ስርዓትን መቀየር ሲሆን የተሃድሶ ግን ሰውን በመቀየር ላይ የተመሰረተ ዘርፈ ብዙ ለውጥን ማምጣት ነው። ተሃድሶ መንፈሳዊ እሴቱና ለመለኮታዊ ስልጣን መካከለኛ ስፍራ መስጠቱ የሃይል ምንጩ ነው። አዲሱ ስፍራ ሲያገኝ አሮጌው ምን አቅምና ለዛ ይኖረዋል? ኅዳሴ (R (Renaissance) ፡ ይህ ከተሃድሶ ጋር እጅግ የቀረበ ዝምድና ያለው ሲሆን ያረጀውንና የተበላሸውን ችላ ብሎ ትኩረቱን የእንደገና ጅማሬ /የዳግም
ብፅዕት ድንግል ማርያም ከገጽ 12የዞረ ብሎ የምሥራቹን አበሰራት። ማርያምም እንዴት ሴት ወንድን ሳታውቅ ልትጸንስ እንደምትችል በመገረም ስትጠይቀው መልአኩም “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፣ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል”(መጋረድ፣ መሸፈን) በማለት ይነግራታል። ማርያምም ከመላኩ ለተሰጣት ምላሽ በእምነት፣ በትህትናና በታዛዥነት ይህን ፈፅሞ በሃሳቧ ያልነበረውን አስገራሚና አስፈሪ ነገር ተቀበለች። ሊያስከፍላት የሚችለውንም የሕይወት ዋጋ ለመክፈልም ቆርጣ እግዚአብሔርን አመስግና መልዕክቱን ከልቧ አኖረች። የዚያን ዘመን አሁን እንደምንኖርበት ዘመን ሰው በማኅበራዊም ሆነ በግል ኑሮው ላይ ልቡ የፈቀደውን አድርጎ ለውጤቱ ተወዳሽም ሆነ ተወቃሽ ያው ግለሰቡ እንደሚሆነው አልነበረም። ይልቁንም በማርያም ዘመን ሰው በግሉም ሆነ በማህበር ከኑሮው ጋር በተያያዘ በሚወስደው ርምጃ ክብሩም ሆነ ውርደቱ ከዘመድ አዝማዱ አልፎ ለነገዱና ለህብረተስቡ የሚተርፍ ነበር። ስለዚህም በአይሁድ ባህል፣ ወግና እምነት ሴት ልጅ ከጋብቻ በፊት ፀንሳ ከተገኘች ዕጣ ፈንታዋ በድንጋይ ተወግራ መሞት ነው። ሴት ልጅ ሳትዳርና የአንድ ባል ህጋዊ ሚስት ሳትሆን ነፍሰጡር ሆና ስትገኝ ወላጆቿ ስለ እርሷ የሚያፍሩበትን ኃፍረት መገመት አያዳግትም። በዚህም ምክንያት ማርያምም ዘመድ ነገዶቿ የሚሸማቀቁበትንና አንገታቸውን ደፍተው
በህብረተሰቡም ሆነ በወገኖቻቸው መካከል የሚኖሩትን አሳፋሪ ኑሮ እያሰበች ልትጨነቅ እንደምትችል የሚስተዋል ነው። ማርያም ከሰርጓ ቀን በፊት አርግዛ ሲያገኛት ዮሴፍ እጇን ይዞ እየጎተተ ከአደባባይ አውጥቶ በድንጋይ ሊያስወግራት እንደሚችል ታውቃለች። ወላጆቿም እንኳን ሊያስጥሏት የመጀመርያ ድንጋይ ወርዋሪዎች እንዲሆኑ ባህሉና የሐይማኖት ህግ እንደሚፈቅድ ጠንቅቃ ትገነዘባለች። በዚህች ድንግል ሴት ልጅ አዕምሮ ውስጥ ከሰማቸው የምስራች ዜና ጋር በተጓዳኝ ሊገቡ ፤ ከልቧ ደጅ የቆሞቱን ፣ የሀሳብ ተግዳሮት የሆኑትን የአይሁድ ሃይማኖት ወግና ባህል ምን ያህል እንዳስጨነቃትና እንዳሳሰባት በቀላሉ የሚታወቅ ይመስላል። ነገር ግን “ጌታ ካንቺ ጋር ነው . . ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ።” ብሎ መልአኩ ሲነግራት ይህንና ሌላውንም አስፈሪ ነገር ሁሉ ትታ “እግዚአብሔርን መፍራት የጥበብ ሁሉ መጀመርያ ቅዱስንም ማወቅ ማስተዋል” (ምሳሌ 9፡10) እንደሆነ አድርጋ በህይወቷ የተለማመደች ሴት ለመሆንዋ የሰማችውን የምስራች አምና “እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ” (ሉቃ 1፡38) በማለት በትህትና መቀበሏ ምግባረ-ሰናይነቷንና መንፈሳዊነቷን ያስረዳል። በአዲስ ኪዳን ውስጥ 19 ጊዜ ያህል የጌታችን እናት ስሟ ተጠቅሷል። በአምላክ የተመረጠች የአምላክ ፀጋ ያረፈባትና በሕይወቷ ከተከሰተው የእግዚአብሔር የማዳን ሥራ ዓላማ ጋር በተያያዘ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብሉይም
ዉልደት ያህል ህብረተሰብን/ማንነትን ነገር ከመበላሸቱ በፊት ወደነበረው መልካም ሁኔታ መመለስ ነው። እውቀት እውነት ነው ደግሞም የለውጥ ብርሃን ብሎ ያምናል። ኪነጥበብ፡ ፍልስፍናን ፈጠራን ያነሳሳል። ከመንፈሳዊነት ይልቅ ሰው ተኮር በመሆኑም በሰው ቻይነትና ልክ የለሽ እምቅ ሃይል ያምናል። አመጽን ግድ ካልሆነ እንደዋነኛ መሳርያ አይወሰድም። በእውቀት ብርሃን ማንኛውም የድንቁርናና የልማድ ጨለማ ይገረሰሳል ብሎ ያምናል። ህዳሴ እውነተኛ ለውጥ ከባህርይ ይልቅ በችሎታ ላይ እንደሚመሰረት ያምናል። በአስራ አራተኛውና አስራምስተኛው ክፍለ ዘመን በደቡብ አውሮፓ የተቀጣጠለው ለውጥ ህዳሴያዊ ባህርይው ሲያመዝን በሰሜን አውሮፓ የነበረው ለውጥ ደግሞ ተኃድሷዊ ነበር ቢባል ማጋነን አይሆንም። ወደ ገጽ 17 ዞሯል ይሁን በአዲስ ኪዳን ስማቸው ከተጠቀሱት ሴቶች ሁሉ የማርያም ድርሻ እጅግ ከፍ ያለና ቀዳሚነት ያላት ቅድስት (ለእግዚአብሔር የተለየች) ታሪክ ያላት እናት ናት። ከማህጸኗ ከተገኘው ከልዑል የአምላክ ልጅ መውለድና፤ ይህም ልጅ በምድርና በሰማይ በሚኖሩት ፍጥረታት ላይ ሊያስከትለው የሚችለውን ቅዱስና እውነተኛ ተፅእኖ የተነሳ ማርያም የከፈለችው ዋጋና መስዋዕትነት ተመን የለውም። “መሲህ” ይወለዳል የሚለውን ትንቢት የሰማው በማርያም ዘመን እስራኤልን ይገዛ የነበረው ንጉስ ሊወለድበት ያለውን ዘመን ቆጥረው እንዲያስረዱት ሊቃውንትን ጠይቆ ካወቀ በኋላ ይኸው “የሴቷ ዘር” በተወለደበት ወራት አካባቢ የተወለዱትን ህጻናት በሙሉ እንዲያርዱ አዋጅ ባስነገረ ጊዜ ኢየሱስን ይዛ ካገር ወደ አገር ስትንከራተት ፀሐይና ውርጭ፤ ብርድና ሙቀት ተፈራርቆባታል። የዱር አውሬው፥ የበረሀው ተናዳፊ እባብ፥ የሽፍታውና የዘራፊው ከአሁን አሁን አገኘኝ የሚለው ስጋት ከራስ ይልቅ በማኅፀን ለተሸከሙት ህጻን ልጅ የእናት አንጀት ምን ያህል እንደሚባባ ለሰው ልጅ ሁሉ ግልጽ የሆነ ጉዳይ ነው። ኢየሱስ አድጎ አገልግሎት በጀመረ ወቅት ደግሞ ትምህርቱ የብዙዎችን ልብ ሲያቀናና ወደእግዚአብሔር ሲመልስ፣ በስጋ ደዌ ይማቅቁ የነበሩትን ህሙማንን ሲፈውስ፤ አጋንንት ያደረባቸውን ከክፉ የመናፍስት አሰራር እስራት ነፃ ሲያወጣ ያዩና መሲህነቱን ወይም አዳኝነቱን ተቀብለው ማመን የተሳናቸው አይሁዳዊያን ምሁራንም ሆኑ
ወደ ገጽ 14 ዞሯል
ገ ጽ14
ብፅዕት ድንግል ማርያም ከገጽ 13 የዞረ
የመጨረሻው መጨረሻ ማቴ24፡ 3 ዶ/ር መንግስቱ ለማ በሕይወታቸው የቤተክርስቲያንን ታሪክ ሊለውጡ የቻሉ ሰዎች የተነሱት ሁልግዜ ትኩረታቸው በክርስቶስ መምጣት ላይ በሚሆንበት ግዜ ነው። በክርስቶስ መምጣት ላይ ትኩረታችሁ በሆነ ግዜ እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ብዙ ነገር ይሰራል። የሚቀርባችሁ አንዳች የለም.....”
ባለሥልጣናት በተቃወሙትና ክስ መስረተው ከፍርድ ወንበር ፊት ባቀረቡት ወቅት የእናቱ የማርያም አዕምሮና መንፈስ በስጋትና በስቃይ ውስጥ ማለፉ የማይታበል ሀቅ ነው። በዘመኑ የነበሩ የአይሁድ እምነት አዋቂዎችና ብዙ ሰዎችም በኢየሱስ አስተምህሮትና አገልግሎት ተገቢ ባልሆነና ቅንነት በጎደለው ዓይን በተመለከቱት ወቅት እናቱን ማርያምን በስድብና በነቀፌታ ይወርፏት እንደነበር ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ሲጽፍ “ከዚያም ወጥቶ ወደ ገዛ አገሩ መጣ ደቀ መዛሙርቱም ተከተሉት። ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኩራብ ያስተምር ጀመር ብዙዎችም ሰምተው ተገረሙና፡- እነዚህን ነገሮች ይህ ከወዴት አገኛቸው? ለዚህ የተሰጠችው ጥበብ ምንድር ናት? በእጁም የሚደረጉ እንደነዚህ ያሉ ተአምራት ምንድር ናቸው? ይህስ ጸራቢው የማርያም ልጅ. .አይደለምን?” ( ማር
6፡1-3) በማለት ኢየሱስ ይናገርበት የነበረውን ፀጋ፣ ያደርጋቸው የነበረውን ተአምራትን ከአንዲት በመካከላቸው ተወልዳ አድጋ ፤ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ወልዳ ያሳደገችውን እያነጻጸሩ የተነጋገሩትን ለማስረጃ ትቶልናል። አይሁዳዊያን በአነጋገር ዘይቤያቸው “የእገሊት ልጅ አይደለምን?” የሚሉት ለዚያ ሰው ዕውቅና ላለመስጠት ሲፈልጉ ቢሆንም እናትንም የዚሁ ስድብ ተካፋይና ለዚሁ ነቀፋ ላገኙበት ሰው ምንጭ ማድረጋቸውም ጭምር መሆኑ ከአይሁድ ጋር ተቀራራቢ ባህል ላለው ለእኛ ሰው ለመረዳት ብዙ አያስቸግረውም። በኃይማኖታቸውም ወግ መሰረት የእናቱን ማህፀን የሚከፍት ወንድ ሁሉ ለጌታ የተቀደሰ (የተለየ) ይባላል ተብሎ እንደተጻፈ በጌታ ፊት ሊያቆሙት ወደ ኢየሩሳሌም መቅደሱ ወዳለበትና በመቅደሱም ወዳለው ካህን ይዘውት በመጡ ጊዜ ስምዖን የተባለው ካህን
ማርያም ልትቀበለውና ልታልፍበት ስላለው ታላቅ መከራ እንዲህ በማለት ተነበየ - “በአንቺም ደግሞ በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል. . . ” (ሉቃ 2፡45) ማርያምም የተቀበለችውና ያስተናገደችው የመከራ ጎርፍ ፈፅሞ ቀላል እንዳልሆነ እርግጠኞች ነን። ሩህሩህና ለሰው ልጆች ሁሉ አዛኝ የሆነው ልጇ ኢየሱስ ምንም ሳይበድል እንደበደለኛ ምንም ሳያጠፋ እንደ ጥፋተኛና እንደ ወንጀለኛ ተቆጠረ። መላው አካላቱ ሰንበር በሰንበር እስኪሆንና ደም እስኪያዘራ ድረስ እጅግ ከባድ የሆነውን የእንጨት መስቀል አሸክመው በጅራፍ ገረፉት። ተፉበት ወገሩትም። እየወደቀና እየተነሳ ወደሚሰቀልበት ስፍራ ወስደው ርቃነ ስጋውን ከዚያ እንጨት ላይ በአይኗ ፊት አንጠለጠሉት። ጎኑን በጦር ወጉት። ይህንን ሁሉ መከራውን ያየችው ወላጅ እናቱ በምን ውስጥ እንዳለፈች ለመረዳት ከጥቂት ዓመታት በፊት ይህን ታሪካዊ ስቅላት በፊልም ተስርቶ ኢየሱስ
ወደ ገጽ 15 የዞረ
የነፍስ መልሕቅ
ዓላማ ይዞ መሰለፍ ዐውደ ጥናት ፓስተር ዶ/ር አበራ ምትኩ ዓላማ ትውልድን….. ቤተሰብን….. ቤተክርስቲያንን… አገልጋይን ያስነሳል…
መልሕቅ
ወ/ ታዲዮስ ማንደፍሮ
ሰው ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገንም ጭምር ለመኖር በሚታመንበት ጉዳይ በዋስትና ዙሪያውን ማጠር ይፈልጋል። ከዚህም የተነሣ በዚህ በአለንበት ምድር ለኑሮው አለኝታና ድፍረት ይሆንለት ዘንድ ያንን የተመኘውን ለመጠበቅ በጽኑ ይተጋል። ይህ ዓለም ዕረፍት የሌለበት የሕይወት መድረክ ነው። በሰው ውስጥ እንደገና የመኖር ተስፋ ለዛሬ ኑሮው በውስጡ የታመቀ ኃይል ሆኖለት ትላንትን አቁሞ ለዛሬ ያሻገረውና ነገን ደግሞ ለመኖር ጉልበት ሰጪ ደጋፊዬ ዋስትናዬ ነው በማለት ይታመንበታል። እንግዲህ ስለ ሰው ስናስብ
ሰው ዘመኖቹ ፈጽሞ እንዲያልቅበት አይወድም። በሕይወት ይኖር ዘንድ ተስፋ ያደረገውን ታምኖ ይጠባበቃል። ያለ ተስፋ መኖር አይቻልምና፤ ሌላው ቀርቶ በጥቂት እንኳን ብናስብ የተፈጥሮ ጉዳይ ሆኖበት ወደ እንቅልፍ ሲሄድ ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተማምኖ ይተኛል። እንደተኛ የሚቀር (የማይነሣ) መስሎ ቢታየው የሚወስደውን እርምጃ ማወቅ አያዳግትም። ይህን ያህል በተስፋ ይመካል። ሰው ተስፋ ማድረጉን ሲያቆም ለመኖር ያለው ጥማት ከመቀዝቀዙ የተነሣ በውስጡ ያለውን የመኖር ኃይል መጦ ሲለሚጨርስ በህይወት መዛልና ተስፋ መቁረጥ ተደምሮበት የህይወት ግቤ ምንድነው? ብሎ እራሱን እንዲጠይቅ ያደርገዋል። ከወዲሁ የተስፋ ረሃብተኛ በመሆኑ ጉዳት ላይ መውደቁ አያጠራጥርም። ለመኖር ለመስራት. . . ወዘተ ህይወትን የማደስና ወደፊት የመንዳት የመገስገስ ብቃት አለው። በአጭሩ ተስፋ የኑሮ ማዕከል ነው። ለዛሬው በምድር ላይ ተስፋ የለሽ ሆኖ መኖር በጥቂቱ ይህን ያህል እውነትና ሐቅ ከሆነ በሕይወት ለዘላለም ተስፋ የለሽ ሆኖ መኖር ደግሞ ሌላው ሰው በቀላሉ የማይወጣው በእጅጉ ሊታሰብበት የሚገባ ከአድማስ ባሻገር ያለ መድረሻ ጉዳይ ነው። በመሆኑም ለዘላለም የሚታመንበትን እውነት ካገኘ በእዚህ ምድር ኑሮውን ያለፍርሃትና ሥጋት ለመምራት ጽኑ መሠረት ይሆነዋል። በውስጥ
ሰውነቱም ይጽናናል። ችግር ቢኖርበትም እንኳን ጊዜያዊ እንደሆነ ስለሚያስብ ለመቋቋም አቅም ይሆነዋል። የሚጠባበቀውን ዕድል እንደሚጨብጥም ስለሚያምን ሞትን የማይፈራ ሕይወትን እያጣጣመ ለመኖር ብርታትን ያገኛል። ኢዮብ 14፡10 “ሰው ግን ይሞትና ይጋደማል ሰውም ነፍሱን ይሰጣል እርሱስ ወዴት አለ?” ይላል። ኢዮብ እንዲጠይቅ ያደረገው ጉዳይ የሰው መጨረሻ እርሱን ጨምሮ ምን እንደሆን ለማውቅ መጓጓቱ ነው፤ አይቀሬ ነውና የብዙ ሰውም ጥያቄ ትላንት፣ ዛሬም፣ ነገም ይህ ነው ቢባል ስህተት አይሆንም። ተስፋ የሚጥልባቸው አሉኝ የሚላቸው ነገሮች ምናልባት ለጥቂት ዘመን በምድር ላይ ብቻ የተወሰነ ሊሆን ይችላል። ሰው በዕውቀቱ፣ በሀብቱ፣ በዘሩ አንዳንዱም በሃይማኖት ተስፋ ያደርጋል። ኢዮብ ግን አሻግሮ ሩቅ ዘመን ብቃት የሆነውን እየተመለከተ የጠየቀው እውነት ሁሉም ሰው ሊያጤኔው የሚገባ አሣሣቢ ጥያቄ ነው።
ወደ ገጽ 15 ዞሯል
ገ ጽ15
ማራናታ!
ብፅዕት ድንግል ማርያም ከገጽ 14 የዞረ
የደረሰበትን ህማምና መከራ ባየን ግዜ ምን ያህል እንደዘገነነን ማሰቡ ብቻ ይበቃል። ማርያም እንዲህ ያለው የመከራ ሰይፍ በውስጧ አልፎ የአካል፣ የመንፈስና የስሜት ስቃይዋ ሲታሰብ ከሴቶች ሁሉ መካከል የተባረክሽ ነሽ የተባለላትን ለመረዳትም ሆነ በተስፋ ለመያዝ የሚያስችል ቅድስና እንዳላት መገመት ብቻ ሳይሆን በውል ማወቅ ይቻላል እላለሁ። የጌታችን እናት ማርያም እግዚአብሔርን ለመታዘዝ እራስዋን የሰጠችበትን መሰጠት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታሪካቸው ጎልቶ ከሚነገርላቸው ሴቶች መካከል ቀዳሚውን ስፍራ የያዘች መልካም
እናት ናት። ከርሷ በኋላ ለሚመጣ ትውልድ ሁሉ ያስተላለፈችው መልዕክት እግዚአብሔርን መፍራት፥ እግዚአብሔርን ማክበር፥ እግዚአብሔርን ሀሳብ ማገልገል፥ ለእግዚአብሔር ዓላማ ዋጋ መክፈል ካለ እስከሞትም ድረስ ታምኖ መሄድ፥ ትህትናና ታዛዥነትን ነው። ህዝበ ክርስትያን ከጌታችን እናት ከቅድስት ማርያም እጅግ ብዙ ልንማረው የሚገባን መንፈሳዊ ትምህርቶች አሉ። ማርያም እግዚአብሔር አምላኳን በመታዘዟ ደስ ያሰኘች፣ ራሷን በቅድስና (ለእግዚአብሔር በመለየት) የጠበቀች፣ የመጣላትን ታላቅ የምስራች በትህትና የተቀበለች፣
የደረሰባትን ታላቅ መከራና ስቃይ ያለማጉረምረም ተቀብላ በወግ (በጨዋነት) ያስተናገደች ነች። በመጨረሻም በአምላኳ ታምና ይህን ታላቅ የዓለም መድኅኒት የሆነውን “ዘር”5ለእግዚአብሔር ክብር ለሰዎች ሁሉ ጥቅም የሆነውን ጌታ ኢየሱስን እንዲመጣ የክብር አገልጋይ ሆነችልን። እግዚአብሔር ስለ ጌታችን እናት ስለ ድንግል ማርያም የተመሰገነና የተባረከ ይሁን። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ከበታች በተመለከተው አድራሻ ሊገኝ ይችላል። solomon4@gmail.com
የነፍስ መልሕቅ ክከገጽ 14 የዞረ እርስዎም ይህንን ጽሑፍ እያነበቡ ሳለ ጥያቄው በውስጥ ሳይፈጠርብዎ እንደማይቀር እናስባለን። መጽሐፍ ቅዱስ ሰው ተስፋ የሌለው ፍጥረት እንዳልሆነ የምስራች ይለናል። የመጨረሻችንን መጨረሻ ሲያጠቃልለው እግዚአብሔር የተናገረንን ብንቀበልና ብናምን እርሱም ታላቅና የማይናወጥ ዋስትና ላይ እንደተመሰረትን የዕብራውያን ፀሐፊ በጥበብ እውነትን በማስረገጥ የተናገረው ቃል ምስክር ነው። “ይህም ተስፋ እንደ ነፍስ መልሕቅ አለን እርሱም እርግጥና ጽኑ የሆነ ወደ መጋረጃው ውስጥ የገባነው።” (ዕብራውያን 6፡19) በቅድሚያ መልሕቅ የሚለውን ቃል እንመልከት “መልሕቅ “ ሲል በወደብ ላይ ያለ አንድን መርከብ የባህር ሞገድና ወጀብ እንዳያንገላታውና ብሎም ከቋጥኝ ጋር አጋጭቶ እንዳያሰምጠው እንዲሁም ከሥፍራው እንዳይወስድ በአንድ ቦታ አጽንቶ እንዲጠበቅ የሚያገለግል መሣሪያ(ዕቃ) ነው። በጥንት ዘመን ባሕረኞች መርከቦቻቸውን በወደብ ላይ ለማቆም ይጠቀሙ የነበረው ትላልቅ ቋጥኝ ድንጋዮችን በአንድነት በመረብ በማሰርና ወደ ባሕር በመጣል ወይም በአሸዋ የተሞላ ከረጢት
እስከ ውስጠኛው የባህር ወለል በሚደርስ ገመድ ወይም ከተገመደ የቁርበት ጠፍር ወደ ባሕር በማጥለቅ መርከቡ ባለበት ስፍራ እንዲጠብቅ ያደርጉ ነበር። በኋላም የብረት አገልግሎት ጥቅም ሲታወቅ በሰንሰለት ላይ የሚታሠር መልሕቅ በመተካቱ ጥቅም ላይ መዋል እንደጀመረ ታሪክ ያስረዳል። መርከብዋ ላለመወሰድና ላለመስመጥ ዋስትናዋ በዚህ ተረጋገጠላት። ክርስቲያኖች በመጀመሪያ የመልሕቅን ፅንሰ ሃሳብ ከየት አገኙት? የሚል ጥያቄ ሊነሣ ይችላል። ታሪካዊ አመጣጡ በተመለከተ ከታላቁ እስክንድር ከብዙ የጦርነት ዘመቻና ድል በኋላ ከአራቱ ጀነራሎች መካከል አንዱ የሥረወ መንግሥቱ ክብር አርማ አድርጎ ይጠቀምበት ነበር። በዚያን ዘመን ይደረግ እንደነበረው ሁሉ የግል ምልክት አድርጎ የተነሳው መልሕቅ ነበር። የሐገር መሪን ደግሞ ግንባር ቀደም አድርጎ በምሳሌ መከተል ሌላው ባህላዊ ጉዳይ በመሆኑ ተቀባይነት አገኘ። የትልቁ እስክንድር የመለያው ልዩ ምልክቱ የፍየል አውራ ምስል እንደነበር ማለት ነው። ይሁን እንጂ በዚያን ጊዜ የነበሩ አይሁድ እንደሌላው ህዝብ ሃሳቡን ስለተቀበሉትና ከማህበራዊ ኑሮቸው ጋር በማዋሃዳቸው እስከ 100 ዓመተ ዓለም ድረስ ከአንዱ ወደሌላው ሲተላለፍ ቆየ። በቤተክርስትያን አካባቢ የተገኘን አፈ ታሪክ በመመርኮዝ አስገራሚ ጹሑፍ ትቶልን ያለፈ የታሪክ ጸሐፊ ሲያስነብበን እንዲህ ይላል። በ100 ዓመተ ምህረት ገደማ አካባቢ ንጉሠ ነገሥት በነበረው “ትራጃን (Trajan) ትዕዛዝ አራተኛው ጳጳስ የነበረውን ክሌይመንት (Clement) በብረት መልሕቅ ላይ
ሲያደርገው ለማመን አስቸጋሪ (አዳጋች) የሆነ ታሪክ እንደሚናገረው ሦስት ማይል ርቀት የነበረው ባህር ጎድሎ ሬሳውን መላዕክት በተዋበ ዕብነበረድ መቃብር እንደቀበሩት ይነገርለታል ( ይህም የመልሕቅን ገናናነት ለማሳወቅ ነበር።) መልሕቅ፣ በተለይም በመጀመሪያዎቹ አማኞች (ክርስቲያኖች) ዙሪያ ለደህንነታቸው መታመኛ ዋነኛ ምልክት (አርማ) ሆኖ ይቆጠር ነበር። ካታኮምብ በተባለ ሥፍራ ቁጥሩ የበዛ የመልሕቅ ቅርጽ እንደነበር ታሪክ ይናገራል። ክርስትያኖች የመልሕቅን ምልክት በቀብር ሥፍራ ፣ በጣት ቀለበት፣ በጌጣጌጦች ----ወዘተ (በዛሬው ዘመን እንደምንጠቀምበት መስቀል ቅርጹ ማለት ነው) እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ በግልጽ የሚጠቀሙበት መለያቸው ነበር። ከዚሁ ጋር (የአሣ፣ የጅልባና የዶልፊንን ቅርጽ) ሌላው ምልክት ነበር፤ ነገር ግን እንደ መልሕቅ ዝነኞች አልነበሩም።ክርስቲያኖች በክርስቶስ ኢየሱስ ላገኙት ደህንነት የተስፋቸው ማረጋገጫ አድርገውት ኖረዋል። በጥንቱ የሮማውያን አገዛዝ ሥር የስደትና መከራ ወቅት ለክርስትያኖች ልዩ ምልክትና ለመሥዋዕትነታችው መግለጫ ነበር። ይህ ብቻ አይደለም ሁል ጊዜ ሲገናኙ የተስፋቸው መልዕክት በመሆኑ ለሠላምታቸው መለዋወጫ “ሠላም ለአንተ ይሁን” በማለት ስሜታችውንና ናፍቆታቸውን በማዛመድ በፍቅር የሚገላለፁበት መሠረት አድርገውት አልፈዋል። ወደ ገጽ 18 ዞሯል
ገ ጽ
16 ጽ16
የኪስ ቦርሳው ( በዕውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ)
ጌታ ስለተስፋ ቃሉ አይዘገይም 2 ጴጥ. 3፡9 ፓስተር ተስፋዬ ሥዩም ….እግዚአብሔር ተስፋን ይሰጣል፤ ተስፋውን በራሱ ጊዜ….መንገድና ኃይል ይፈጽማል….
ባንድ ቆፈናም ብርዳማ ቀን ወደቤቴ ስጣደፍ የሆነ ሰው መንገድ ላይ የጣለው የኪስ ቦርሳ ቢያወላክፈኝ አነሳሁትና ባለቤቱን ለማግኘት የሚያስችሉኝ መታወቂያዎችን በማግኘት ስልክ ልደውልለት በማሰብ ውስጡን ገለባብጬ አየሁት። ቦርሳው ውስጥ የነበረው ግን ሶስት ብርና ላመታት የተቀመጠ የሚመስል ጭምድምዱ የወጣ ደብዳቤ ብቻ ነበር። ፖስታውም እርጅትጅት ከማለቱ የተነሳ ከላኪው አድራሻ በስተቀር ምንም የሚነበብ ነገር አይታይበትም። የሆነ ፍንጭ ባገኝ ብዬ ፖስታውን መክፈት ጀመርኩ። የተጻፈበትን -----1951 ዘመንን አየሁ። ደብዳቤው ከተጻፈ 60 ዓመት ገደማ ነው ማለት ነው። ደብዳቤው በቆንጆ የአንስታይ እጅ ጽሁፍ ሰማያዊ ቀለም በስሱ የበነነበት በሚመስልና በግራ ማዕዘኑ ላይ ሚጢጢ አበባ ባለችበት ወረቀት ላይ የተጻፈ ነው። ደብዳቤው “ውዴ ፍቅሬ” እያለ ለደብዳቤው ተቀባይ ለሚካኤል የተጻፈ ሲሆን ጸሃፊዋ እናቷ ስለከለከሏት ከእንግዲህ ልታየው አለመቻሏን ጠቅሳ ያም ቢሆን ምንግዜም እንደምታፈቅረው የገለጸችበትና ሃና የሚል ፊርማ የተቀመጠበት ነው።
ውብ ደብዳቤ ነበር! ታዲያ ምን ያደርጋል ሚካኤል በሚለው ነጠላ ስም በስተቀር ባለቤቱ በምንም ሁኔታ ሊታወቅ የሚችልበት መንገድ አልነበረም። ምናልባት ማዞሪያ ብደውል በፖስታው ላይ ባገኘሁት የላኪው አድራሻ የተመዘገቡ ቁጥሮችን ሊሰጡኝ ይችሉ ይሆናል ብዬ አሰብኩ።ግዜም ሳልወስድ “ ማዞሪያ! “ አልኩ ደውዬ። “ምናልባት ይሄ ያልተለመደ ጥያቄ ሊሆን ይችላል መንገድ ላይ ወድቆ ያገኘሁትን ቦርሳ ባለቤት ለማግኘት እየሞከርኩ ነውና በፖስታው ላይ በተጻፈው አድራሻ የተመዘገበ የስልክ ቁጥር ልትነገሪኝ የምትችልበት መንገድ ካለ” ብዬ ጠየቅኳት። እሷም ከአለቃዋ ጋር ብነጋገር የሚሻል እንደሆነ ጠቆመችኝና ትንሽ ካመነታች በኋላ ሀሳቧን ቀይራ “ በዚያ አድራሻ የተመዘገበ ስልክ አለ ነገር ግን ያንን ስልክ ልሰጥህ አልችልም “ አለችኝ። ቀጥላም ያንን ስልክ ደውላ ታሪኩን ነግራቸው መገናኘት ይፈቅዱ እንደሆን ልትጠይቃቸው ቃል ገብታልኝ ስልኩን ሳልዘጋ እንድጠብቅ ነገረችኝ ። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ስልኬ ላይ ተመልሳ “ ሊያናግሩህ ፈቃደኛ የሆኑ ወገኖች አሉ!” ብላ አገናኘችኝ። በዚያኛው ስልክ ጫፍ ያሉትን ሴትዮ ሃና የምትባል ሰው ያውቁ እንደሆን ጠየቅኳቸው። “ እህ! ይህንን ቤት የገዛነው ሃና የምትባል ልጅ ካላቸው ቤተሰቦች ላይ ነው። ይህ ግን የሆነው የዛሬ 30 ዓመት ነው!” አለችኝ በሚያቃትት የተቆራረጠ ድምጽ። “ያ ቤተሰብ ባሁኑ ግዜ የት
ወደ ገጽ 19 ዞሯል
67 ደቂቃዎች ..... ከገጽ 11 የዞረ
የጸጋ ስጦታ 1 ቆሮ. 1፡7 ፓስተር ዶ/ር በድሉ ታንቁ
…. ሥራ እየሠሩ ጌታን የሚጠብቁ ጸጋ አይጎድልባቸውም
መልሕቅ
መልሕቅ፦ በውጭ ሀገር የት የት አገልግለሻል? ሒሩት፦ መጀመሪያ ውጭ ሀገር መሄድ የጀመርኩት አፍሪካ ውስጥ ነው። ናይሮቢ አገልግያለሁ፣ ቀጥሎ ዱባይ፣ከዚያ በኋላ ቀጥታ ወደ አሜሪካ ነው የሄድኩት። አሜሪካ ዋሽንግተን ዲ ሲ ፣ ኒውዮርክ፣ ቦስተን፣ ሚንያፖሊስ፣ ኢንዲያናፖሊስ፣ ኦክላንድ፣ ሎስ አንጀለስ፣ ሲያትል፣ሳን ሆዜ፣ ዴንቨር፣ ዳላስ ፣ቺካጎ፣ ሌሎችም አሉ አሁን ማስታወስ አቃተኝ። ከአውሮፓ ደግሞ ለንደን ፣ በርሊን፣ ፍራንክፈርት፣ ሙኒክ ሽቱት ጋርት፣ ኮሎኝ ጣሊያን፣ ሆላንድ፣ ቤልጅም፣ ስዊድን፣ አውስትራሊያ.... መልሕቅ፦ በቃ በመላው አለም ማለት ይቀልሻል.... ሒሩት፦ አዎን ! (ሳቅ) እግዚአብሄር ይመስገን! መልሕቅ፦ የሚያናድድሽ ነገር ምንድነው? እንዴትስ ራስሽን ታበርጃለሽ? ሒሩት፦ በምናደድበት ግዜ በአንደበቴ ማውጣት አልፈልግም። ዝም ነው ። ለቅሶም አለ። ማንም ሰው ሳያየኝ ሄጄ አለቅሳለሁ። በዛው እተወዋለሁ ። ደግሞ ዕርቅ ከተፈለገ ዕርቅ ለማድረግ ግዜ አይፈጅብኝም። ጌታ የሰጠኝ ፀጋ ነው... መልሕቅ፦ መልሕቅ የሚገርምሽ የሚቀጥለው ጥያቄዬ ስለ ይቅርታ ነበር በጣም ጥሩ ነው በዛው ቀጥዪ... ሒሩት፦ (ሳቅ)... ይቅርታ ሳደርግ ሙልጭ ብሎ ይወጣልኛል። ይቅርታ ያለማድረግ ለኛው ለራሳችን መጥፎ እንደሆነ “ሲዖል ሲገለጥ” የሚለውን መጽሐፍ አንብቤ
በጣም ብዙ ትምህርት አስተምሮኛል ። እሱን አንብቤ “ዕውነት ነው! ምንድነው የሚጎዳኝ እኔን ?” አልኩ። በጣም ትንሽ ልጅ ብትሆን እንኳን በድያት ከሆነ ጉልበቷ ላይ ለመውደቅ ግድ የለኝም። ግን እኔነት ካለ ይቅርታ ማድረግ ከባድ ነው። አይቻልም። በጣም! .... አጅሬ ይመጣና “እንደዚህ ብላሽ እንዴት እንደዚህ ትሆኛለሽ ....እንደዚህ አድርጋሽ?” ይላል። ይሄ እኔጋ የለም ! ምክንያቱም የራሴን በረከት ነው የሚወስድብኝ። በጣም የሚያስቸግር ነው ይቅርታ ያለማድረግ። ያለ ይቅርታ ቤ/ክ ብንሄድ፣ ወንድም እህቴ ብንባባልም አይሆንም። ያቺን ነገር አውጥተን መጣል አለብን። እኛ ነን ይቅርታ አድራጊዎች። ተበድለንም። መልሕቅ፦ እስከ ዛሬ ምን ያህል ዝማሬዎች ዘምረሻል? ሒሩት፦ ሶስት ክሮች ወጥተዋል። እያንዳንዳቸው አስር መዝሙሮች ነው የያዙት። ሰላሳ መሆናቸው ነው። አሁን ደግሞ ብዙ አሉኝ የተቀመጡ እግዚአብሄር እየሰጠኝ ስለሆነ። ወደፊት ጌታ ቢፈቅድ እንግዲህ አንድ ነገር እናደርጋለን። እስካሁን ግን ውጭ አገርና ሀገሬ ምድሬም ውስጥ በመዞር ጉዳይ ተይዤ ነበር። አሁን ግን በደንብ ፈጽሞ እስኪሻለኝ ድረስ ብዙ አልወጣሁም። አሁንም ላገለግለው
እወዳለሁ ጌታን። መልሕቅ፦ ጌታ በኢትዮጵያ ላይ የፈለግሽውን እንድታደርጊ የ 24 ሰዓት መብት ቢሰጥሽ ምን ታደርጊበታለሽ? ሒሩት፦ በሰጠኝ ጥበብ በሰጠኝ ፀጋ ህዝብ በሙሉ እንዲድን እወዳለሁ። ጓደኞቼ ሁሉ እንዲድኑ። ሁሉ የእግዚአብሄር ባርያ እንዲሆን እወዳለሁ። ያንን አደርጋለሁ ይሄ ነው የኔ ምኞቴ። መልሕቅ፦ ከዘማሪዎች ይበልጥ የሚባርክሽ መዝሙር የማን ነው? ሒሩት፦ ሁሉንም እወዳቸዋለሁ። ዘማሪ ሲባል በኔ ግምት እግዚአብሄር ነው ያስነሳቸው። መቼም ከእያንዳንዱ ዝማሬ ለልብ የሚሆን ይኖራል። ለሁሉም የሚሰጠው መንፈስ ቅዱስ እግዚአብሄር ነው። እናም በድሮ ግዜ እኔ በጌታ ሳልሆን የነበሩት ዘማሪዎችንም እወዳቸዋለሁ። አሁንም ደግሞ እግዚአብሄር ብዙ ድንቅ ዘማሪዎችን አስነስቶልናል። ሁሉንም በጣም እወዳቸዋለሁ። ምክንያቱም ሁሉም ቢያንስ ከአስሩ ዝማሬዎች ውስጥ አንድ ሶስቷ ለኔ ሕይወት ትሆነኛለች። እግዚአብሔር አሁንም ያበርታቸው!
ወደ ገጽ 24 ዞሯል
ገ ጽ17
ማራናታ!
ለውጥ - አማራጭ የሌለው ምርጫ ከገጽ 13 የዞረ ስለ ለውጥ ተግባራዊ ምክር ለአበሾች ከግል እስከ ሃገር፡ ብዙ ዘመን ሌሎች ቢቀየሩ የህዝባችን ችግርና ጉስቁልና እንደሚወገድ ተናግረናል። እንዴትና ወዴትም መቀየር እንዳለባቸው ደስኩረናል፡ ዛሬ ግን እኛ ራሳችን ያንን ለውጥ መለወጥ እንዳለብን ልንገነዘብ ይገባናል። መቀየር እንዴት ጠቃሚ መሆኑን ብቻ ሳይሆን ምንኛም አስቸጋሪ መሆኑን መረዳትና ለሌሎች ማዘን እችል ዘንድ መቀየር ያለብኝ እኔ ነኝ። አብዮትና የትጥቅ ትግል፣ ጦርነትና ፍጅት፣ ቅናትና ምቀኝነት አገር ቢቀይር እኛ የት በደረስን? እስኪ አሁን ወደተሃድሶና ንጥቀት ራሳችንን እናደግድግ። ወደእግዚአብሄር በሙሉ ልብ መመለስ፣ ራስን ሳይሰስቱ ላመኑበትና እውነት ለሆነው ነገር መሰጠት፣ እውነትን መራብና ለተረዳነውም ነገር መታዘዝ ይገባል። ከባዶ ኩራትና ከድብቅ የበታችነትና ያለመቻል ስሜት ሳንላቀቅ ማኅበረሰባዊ ለውጥ አይመጣም። ትህትናና ድፍረትን መማር ለመለወጣችን ቁልፍ ሳይሆን አይቀርም ። ንጥቀት ((Transfor Transform Transformation)፤ ation) አላማው ነገሮችን ወደነበሩበት ሁኔታ የማደስ ብቻ ሳይሆን መድረስ ወዳለባቸው ፍጽምናና ልህቀት ወዳለው የማንነት ምልአትና የውበትና ድምዳሜ መለወጥ ነው። ልህቀትና ፍጽምና ዘላለማዊ ናቸው አሁናዊም። ንጥቀት ሁሉን ነክ ስር ነቀልና ውብ ለውጥን ያልማል። ተኃድሶና ንጥቀት የመጀመሪያ ደረጃዎች ናቸው። ንጥቀት ከዝቅተኛው ዝቅጠት ነጥቆ ወደማይደረስበት ልህቀት ማምጠቅ ገዢ ግቡ ነው፡፡ ከአቅመ ቢስ ትል የምታምርና በነጻነት የምትበር ዉብ ቢራቢሮን መንጠቅ! በንጥቀት ያለው ሃይል መለኮታዊ ሲሆን፤ አይቻልም የሚባል ነገር የለም። ፍጥረት ንጥቀትን ይናፍቃል። ንጥቀት አንዳች ንዝረት ያለው ሁለንተናዊ ለውጥ ነው። ማብቂያና ግድፈት የለበትም። ንጥቀት ይጋባል፡፡ በእውነተኛ የንጥቀት ለውጥ
ዉስጥ ያለፉ ያለብዙ ትግል ሰፊ ተጽዕኖና ለውጥን ማሳደር ይችላሉ። ዛሬ በአለም ላይ ንጥቀት የሁሉ ግብና ምትሃታዊ ቃል ሆኖአል። ይህ የሰዎችን የልብ ጥማት ያሳያል። ንጥቀታዊ ለውጥ የማያስፈልገው ይኖር ይሆን? ከታላላቅ የለውጥ ሰዎች አንደበት ስለለውጥ በአለም ላይ እንዲሆን የምትፈልገውን ለውጥ አንተ ራስህ ሁነው። ጋንዲ መልካም ወደሆነ ነገር ሁሉ ራስህን ለመለወጥ ትጋ። አርስጣጣሊስ ሁል ጊዜ ደስተኛና ጥበበኛ የሆኑ ሰዎች ያለማቋረጥ በለውጥ ሂደት ዉስጥ ያሉ ብቻ ናቸው። ኮንፊሺየስ ሁሉ ነገር ጠፊና ተለዋዋጭ እንደሆነ ስትረዳ ምንም ነገር የሙጥኝ ብለህ አትይዝም። ከዚህም የተነሳ ለሞትም እንኳ ያለህን ፍርሃት ካሸነፍክ ደግሞ ያኔ ለመለወጥ የሚያዳግትህ ነገር አይኖርም። ላኦ ዙ ሰዎች የሚቃወሙት እኮ ለውጥን አይደለም። የሰዎች ዋነኛ ተቃውሟቸው በራሳቸው ላይ ሊመጣ የሚችለውን ለውጥ ነው። ፐተር ሲንጅ ጥቂት ነገሮችን ብትለውጥ፤ ብዙ ጠላት ነው የምታፈራው። ዊልሰን ውድሮው ካልተለወጡ ስፍራዎችና ሰዎች ይልቅ እኛ ራሳችን ምን ያህል እንደተለወጥን ልንረዳበት የምንችልበት እድል አይገኝም። ኒልሰን ማንዴላ ሌሎችን ከልብ ማክበርና በመስዋእትነት ማገልገልም መማር ያስፈልገናል። በአለም ዙሪያ አስደናቂና ፈጣን ለውጥ እየተካሄደ ነው። ይህ የዕድል መስኮት ሳያመልጠን ፍርሃትና ጥርጣሬውን አሸንፈን ለመለወጥና ለመለወጥ ወደጨዋታው ሜዳ እንጋበዛለን። ቅንነት፣ እምነት፣ አንድነትን መኮትኮት ቅድመ ሁኔታ ነው። ከቤትና ካካባቢ እንጀምር። በህዝባችን ዘንድ ትልቅ የለውጥ ረሃብ አለ ከገጠር እስከ ከተማ፤ ከወጣት እስከ አዛውንት፡ ከማይም እስከ ሊቅ፤ ታዲያ ከዚህ የተሻለ ጊዜ መቼ ይመጣል? ያለንን እንስጥ፤ እውቀታችንን እንጨምር፤ እንወያይ፤ በህብረት መስራት እንጀምር፤ መልካምን እንናገር። ተቃውሞን ለምን እንፈራለን? ለውጥ
ያለተቃውሞ አይሆንም። በለውጥ ዘመን እንዳለመለወጥ ድህነት በለውጥ ውስጥም ተሳታፊ እንዳለመሆን ባዶነት የለም። የለውጥ እንቅፋት መሆን ደግሞ ከሁሉ የከፋ የህይወት ብክነት ነው። ከባከነ ህይወት ደግሞ የተደፋ ዉሃ ይሻላል። እንደለውጥ ምን ጥሩ ነገር አለ። እንደመለወጥስ ምን አስደሳች የህይወት ልምምድ ይገኛል። እንደኛ ህዝብስ ለውጥ የሚያስፈልገው ምን ህዝብ አለ??? እንግዲህ በለውጥ እርሻ እንገናኝ። ያውም የኔ፣ ያንቺ፣ ያንተ፣ የርሶ የሁላችን ህይወት ... ዛሬን እስከምንሞት! ለመታደስና ለንጥቀት! ስለለውጥ የመጨረሻና ቁልፍ ቃል፡ የእውነተኛ ለውጥ ምንጭና ባለቤት እግዚአብሄር ነው። ሰው ራሱን መቀየር አይችልም። እግዚአብሔርም በግድ አይቀይረውም። ለውጥ በሰው ፈቃደኝነት ላይና በእግዚአብሔር ሃይል ላይ የተመሰረተ ነው። ይህም ፈቃደኝነት ዋነኛ መገለጫው የማያቋርጥ ጸሎት ሲሆን የእግዚአብሔርም ሃይል አላማው የተለወጠን ህይወት እንድንኖርና የለውጥ ወኪሎች ሆነን ለሰዎች ሁሉ መልክተኛ እንድንሆን ነው። የማይጸልይ ሰው አይለወጥም ጸሎት ግን የማይለውጠው ምንም ነገር የለም። ጸሎት የእግዚአብሔር የመለወጥ ሃይል ደካማ በሆነ ሰው ክንድ ዉስጥ ሲገለጥ ነውና። በጸሎት እግዚአብሔር ግለሰቦችን፣ ቤተሰቦችን፣ ሁኔታዎችን፣ ህዝብንና ትውልድን ብሎም ሃገርን ይለውጣል። የእግዚአብሔር ቃል እግዚአብሔር አለምን የፈጠረበት ብቻ ሳይሆን በዘመናት መካከል የመለወጥ ስራውን የሰራበት የእስትንፋሱ ሃይል ነው። በመንፈሱ ሃይል እንደተነገረ ቃል ምን የሚለውጥ ሃይል ይኖር ይሆን?? ለውጥ የእግዚአብሔር ዋነኛ አጀንዳ ነው። እርሱ ሰውንና ፍጥረቱን ሁሉ በመለወጥ ስራ ላይ ነው? አንተስ? አንቺስ? ይህንን ዘመን የለውጥና የድል ያድርግልን!! ቸር ይግጠመን
የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ከበታች በተመለከተው አድራሻ ሊገኝ ይችላል። mirumercy@yahoo.com
ገ ጽ18
የነፍስ መልሕቅ ከገጽ 15 የዞረ
ትጉና ጸልዩ ሉቃስ 21፡36 ፓሰተር እንድርያስ ሐዋዝ
…. ብዙ ሰው ስለጸሎት ያውቃል እንጂ ጸሎትን አያውቅም
በንጽህናና በቅድስና መጠበቅ 1ኛ ዮሐንስ 3:3
ታዲዮስ ማንደፍሮ “....አዳምና ሔዋንን
ተመራማሪዎች (Archaedlogists) በአንድ ሥፍራ ወደ 70 የሚሆኑ መልዕክታዊ ትርጉም ያዘሉ የመልሕቅን አገልግሎት የሚያስተጋባ ቅርስ እንደተገኘ ለትውልድ መዝግበው ይዘውታል። ለክርስቲያኑ ኅብረተሰብ ስለ ምን መልሕቅ ይሰጥ ከነበረው ምሳሌያዊ ምልክት ቀስ በቀስ አገልገሎቱ ሊደበዝዝ ቻለ? ብለን ማሰባችን አይቀርም። ይህን በተመለከተ ብዙ ምክንያቶች ይነገራሉ። ይሁን እንጂ ምን ይባል ምን ከሞላ ጐደል ከ300 ዓ.ም በኋላ ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይታል። ከዚያም በኋላ በክርስቲያኑ ላይ ስደትና መከራ በመነሳቱ የድብቅ መለያቸው አድርገው መጠቀምን እርግፍ አርገው ተዉት። ቀጥሎም በቀስጢኖስን የድል መስቀል ገናናነት ምክንያት ለክርስቲያኑ ቤተሰብ መልሕቅ የባህር ወጀብ ድነት መነቃቂያ ምንጭ የነበረው ምሳሌነቱ በመስቀል ተተካ። ይሁን እንጂ እስከ 1600 ዓ.ም ድረስ ሳይታይ ከቆየ በኋላ በተከታዩ ዘመን እንደገና በማንሠራራቱ ጥቂትም ቢሆን በመቃብር ሐውልቶች ላይ መታየት ጀምሮ ነበር። በአጠቃላይ መልሕቅ የታሪክ ድሃ አይደለም ባለጠጋ እንጂ፤ ምክንያቱም በዝምታ የማይታለፍ ሰፊ ታሪክ ያካበተ ለመሆኑ ፈላስፋዋችና ባለቅኔዋች ስለ መልሕቅ ብዙ ብለዋል። ያንን ሁሉ ማቅረብ
ከገነት ያስወጣቸው ሌላ ጉዳይ አይደለም ኃላፊነት ነው። ...ይሄም የሰው ሁሉ ችግር ነው”
ባንችልም ለቅምሻ በጥቂቱ የተጨመቀ ከታሪክ ማህደር ካልን በኋላ ወደ ተነሣንበት መንፈሳዊ ሃሳብ እናልፋልን።
በመሄድ በራሱ በእግዚአብሔር ላይ ይታሰራል። ይህም የነፍስ መልሕቅ እርግጠኛና ጽኑ ነው። እርግጠኝነቱ የነፍስ መልሕቅ የእግዚአብሔር እግዚአብሔር በጸጋው በእኛ ከሰራው የተነሳ የማይናወጠው ምህረቱ፣ ህዝብ ለተስፋቸው መድረሻ ዋስትና በምን ሥራ መንገድ እንደሚቀበሉ ለማሳየት የተገለፀበት ጠንካራና አስተማምኝ ነው። ጽናቱ ደግሞ በዓላማ ላይ እንደጸና፣ አጥብቆም ሀሳብ ነው። እግዚአብሔር አምላክ እንደሚይዝ መልሕቅ ወደ መጋረጃው በጌታችንና በመድሃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል የሰጠውን ድነት የተቀበሉና ውስጥ የሚገባና በዘመናት ዓለት ላይ ይታሰራል። ይኸውም በመጋረጃው ያመኑ ሁሉ በመንግሥቱ ውስጥ ውስጥ የገባና በክርስቶስ ላይ የታሰረ የእግዚአብሔር ቤተሰብ ለመሆናቸውና ያም ነው። እርሱም የአማኞችን ተስፋ የያዘ ዕውነትና የማይነቃነቅ፣ ፈጽሞም የማይሻር፣ የተደላደለ ተስፋ በዚያ የቀረላቸው መሆኑን መልሕቅ ነው። አማኞች ምንድነው ተስፋ የሚያደርጉት? በመጋረጃው ውስጥ ያስረግጣል። እንደማይታይ ክብር፣ ኢየሱስ ለማጠቃለያ ይህን ሀሳብ አስመልክቶ ጥቂት በመጋረጃው ውስጥ የማይታየው ነገሮችን እንመልከት፦ የተስፋቸው መሠረት ነው። በነፃ የተሰጠው የእግዚአብሔር ጸጋ፣ 1ኛ) መልሕቅን ከላይ እንደተመለከትነው በክርስቶስ የተከፈለው ዋጋና የተገኘው ተምሳሌታዊነት አለው። ነፍሳችንም ብዙ እርቅ፤ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ነገሮችን እንደተጫነች መርከብ አድርገን የተሰራው ሥራ የአማኞች የተስፋ ልንወስዳት እንችላለን፤ እንዲሁም መንግስተ መሠረት ደግሞም የተስፋቸው ጽናት ሰማያትን ደግሞ የጉዟችን መድረሻ ነው። ክርስቶስ ለአማኞች በብዙ (destination) ወደብ። የዚህን ዓለም አክብሮት ዓላማቸውና የተስፋቸው መከራና ስደት መርከብን እንደሚያናውጥ መሠረት መሆኑን ሐዋሪያው ቅዱስ ነፋስና ማዕበል ተደርጎ ሊወሰድ ይቻላል። ጳውሎስ ገልጾታል። ዛሬ የእርስዎ የነፍስ 2ኛ) ዘወትር በማያቋርጥ ውጊያ መካከል ስለምንገኝ እንዳንናወጥ ሥፍራችን ሳንለቅ ባለንበት ሥፍራ እንድንቆይ የሚያስችለን መልሕቅ ያስፈልገናል። 3ኛ) የምስራቹ ቃል የነፍሳችን መልሕቅ ነው። ይህም ቃል ጋሻና መከታ እንዲሁም መሪያችን ነው።
መልሕቅ በየት አለ? “የተስፋን ቃል የሰጠው የታመነ ነውና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ።” (ዕብራውያን 10፡23) አሜን!
4ኛ) የክርስቲያኖች የነፍስ መልሕቅ ወደ ላይ ወደ እውነተኛይቱ ሰማያዊት መቅደስ
ተዘጋጅታችሁ ኑሩ ማቴ. 24፡44 “ማራናታ ስንል …ከእያንዳንዳችን ሕይወት የሚጠበቅብን ነገር አለ፤ ንቃት፣ በመጠን መኖር፣ መመካከር፣ መተናነጽ .....”
ወንድም ፍፁ ፍፁም ሐዋዝ የጉባኤው አገልጋይ
መ ልሕቅ
ገ ጽ19
ማራናታ!
ታላቁ ስጦታ
(ከአብርሃም ዳምጤ ) ሴንት ልዩስ
የዛሬው ታሪክ በሀገራችን ሲነገር ከቆየ አንድ ታሪክ ጋር ተመሳሳይ ሲሆን የምናቀርበው በአንድ ወቅት “ሎስ አንጀለስ ታይምስ” የተባለ ጋዜጣ ለንባብ ያበቃውን ነው። ነገሩ እንዲህ ነው። ቢል የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ለማጠናቀቅ ጥቂት ወራት ሲቀረው ወደ አባቱ ቀረብ ብሎ “አባቴ ሆይ ትምህርቴን ስጨርስ የምትሸልመኝ ምንድነው?” በማለት ይጠይቃል። አባትየውም ቢል ጎበዝ ተማሪ እንደሆነ ስለሚያውቅ ትምህርቱን ጨርሶ ሲመረቅ አንድ ዘመናዊ መኪና ሊገዛለት ቃል በመግባት በዕለቱ መኪናውን የሚገዛበትን ቼክ እንደሚያስረክበው ይነግረዋል። በቀሩት ወራት ቢል ስለሚሰጠው ቼክ ስለሚገዛው መኪና እያሰላሰለ ከቆየ በኋላ በግዜው ተመርቆ ቤቱ ገባና ከአባቱ የሚበረከትለትን የቼክ
ስጦታ መጠባበቅ ጀመረ። በዚህን ግዜ አባትየው ልጁን በደስታ ተቀብሎ ከሳመውና መልካም ምኞቱን ሁሉ በአባታዊ ፍቅሩ ከገለፀለት በኋላ አንድ ትልቅ የታሸገ ፖስታ ያበረክትለታል። ቢል ከአባቱ የተገባለትን ቃል ስላስቸኮለው ወዲያው የታሸገውን ፖስታ ሲከፍት ውስጡ ያገኘው መጽሀፍ ቅዱስ ነበር። የተሰጠው ስጦታ የስጦታዎች ሁሉ ቁንጮ የሆነው መጽሐፍ ቅዱስ በመሆኑ መደሰት የነበረበት ቢል ተበሳጭቶ ስጦታውን በመወርወር ቤቱን ጥሎ ጠፋ። ወዴት እንደሄደ ባለመናገሩ ቤተሰቦቹ ሁሉ በጣም አዘኑ። ሳያገኙትም ብዙ ግዜ ቆዩ። ከረጅም ግዜ በኋላ የቢል አባት ይሞታል። ልጁ ቢልም ያባቱን መሞት ሰምቶ ወደ ቤተሰቡ በመምጣት ካዘነና ካለቀሰ በኋላ ቤቱን እየተዘዋወረ ሲመለከት ለምርቃቱ ከአባቱ የተበረከተለትን መጽሐፍ ቅዱስ መደርደሪያ ላይ ይመለከታል። በዚህን ግዜ “ይህ ከአባቴ የተሰጠኝ ስጦታ ከእኔ ጋር መሆን አለበት” ብሎ አነሳውና ሲከፍተው ውስጡ አንድ ቼክ አገኘ። በላዩም ከአባቱ ቃል የተገባለትን መኪና መግዛት የሚችል መጠን ገንዘብ ተጽፎበት ነበር።ከዚህ በኋላ ቢል ቀድሞ ባደረገው ስህተት ተፀጽቶ የአባቱን ስጦታ አክብሮ በመቀበል ብሩን ለችግረኞች ከሰጠ በኋላ መጽሐፍ ቅዱሱን በየግዜው በማንበብ መንፈሳዊ
ሕይወቱን መምራት ጀመረ። በምድር ላይ ለሰው ልጅ የተሰጠ ትልቁ ስጦታ መፅሐፍ ቅዱስ ነው። ይህንንም ስጦታ የሰጠን ሰማያዊ አባታችን ልዑል እግዚአብሔር ነው። መፅሐፍ ቅዱስን መመሪያችን ብናደርግ ባዶነታችን ይሞላል፤ ችግራችን ይቃለላል፤ ከበሽታችን እንፈወሳለን፤ ፍፁም ንፁህ እንሆናለን። በሀብት ብንከብር ፤ በዕውቀት፣ በጉልበት ፣በስልጣን ታዋቂዎች ብንሆን የእግዚአብሔር ቃል በኛ ዘንድ ከሌለ ሁሉ ነገራችን ከንቱ ነው። የእግዚአብሄር ቃል ሕይወት ነው። የእግዚአብሄርን ቃል እናንብብ እንስማ፣ በእግዚአብሄር እንመራ። ለሁሉም አምላካችን ይርዳን። አሜን! “ከአዕላፋት ወርቅና ብር ይልቅ የአፍህ ህግ ይሻለኛል” መዝ 118 ፦ 72 ከአነበብኩት ምንጭ Spring of love No 753
የኪስ ቦርሳው ከገጽ 16 የዞረ እንዳለ ያውቃሉ? አልኳቸው። “ከብዙ ዓመታት በፊት ሃና እናቷን መጦሪያ ቤት እንዳስገባች አስታውሳለሁ” ካሉ በኋላ “ ምናልባት መጦሪያ ቤቱን ብትገናኝ ልጃቸው የት እንዳለች ማፈላለጉን ሊረዱህ ይችላሉ”አሉኝ። የጡረተኞቹን ቤትንም መጠሪያ ስም ነገሩኝና ደወልኩ። አሮጊቷ የሀና እናት ከጥቂት ዓመታት በፊት እንደሞቱና ልጃቸው ትኖርበታለች ብለው የሚያስቡት ቤት ስልክ ቁጥር ግን ሊኖራቸው እንደሚችል ነገሩኝ። ካመሰገንኳቸው በኋላ በሰጡኝ ቁጥር ደወልኩ። ስልኩን የመለሰችልኝ ሴት ሃና እራሷ በመጦሪያ ቤት እንደምትኖር ገለጸችልኝ። ለራሴው ነገሩ ሁሉ የማይረባ ነው ብዬ አሰብኩ። 3 ብርና 60 ዓመት የሆነው ደብዳቤን የያዘ የኪስ ቦርሳን ባለቤት ማግኘትን ስለምንድነው ትልቅ ነገር አድርጌ የወሰድኩት? ብዬ ራሴን ጠየቅኩ።የሆነ ሆኖ አላቆምኩም ቀጠልኩ። ሃና ትኖርበታለች ወደተባለው ጡረተኞች ቤት ደወልኩ። ስልኩን ያነሳው ሰውዬ “ አዎ ሀና እኛጋ ነች” ብሎ ነገረኝ። ሰዓቱ ከምሽቱ 4 ሰዓት ቢሆንም መጥቼ ላያት እችል እንደሆን ጠየቅኩት።
እያመነታ “ ይሁና ! ዕድልህን መሞከር ከፈለግክ በመዋያ ክፍል ውስጥ ቴሌቭዥን እያየች ሳትሆን አትቀርም” አለኝ።አመስግኜው ወደ ጡረተኞች ቤቱ መኪናዬን አስነስቼ ነጎድኩ። በሩ ላይ ከማታ ተረኛዋ ነርስና ከጥበቃው ዘብ ጋር ሰላምታ ተለዋወጥንና ወደዚህ ግዙፉ ሕንጻ 3ኛ ፎቅ ላይ በአሳንሳር ወጣን። በመዋያ ክፍል ውስጥ ነርሷ ከሃና ጋር አስተዋወቀችኝ። ሃና አስደሳች ባለብርማ ጸጉር ፣ባህልን ተከታይ የሆኑ ፣ ደማቅ ፈገግታ ከሚያበሩ ዓይኖች ጋር ያላቸው ሴት ናቸው ። የኪስ ቦርሳውን ማግኘቴን ነገርኳቸውና ደብዳቤውን አሳየኋቸው። ከመቅጽበት ሰማያውን ወረቀትና ሚጢጢዋን አበባ ሲያዩ በረጅሙ ተነፈሱና “ ይሄ ደብዳቤ ከሚካኤል ጋር ለመጨረሻ ግዜ የተገናኘሁበት ነው” ካሉኝ በኋላ ፊታቸውን አዙረው በጥልቅ ሃሳብ ውስጥ ነጎዱ። ከሃሳባቸው ሲመለሱም በለስላሳ ድምጽ “ በጣም አፈቅረው ነበር፤ ግና ገና የ16 ዓመት ልጅ ነበርኩና እናቴ ለፍቅር ልጅ እንደሆንኩ ነበር የተሰማት። እህ! በጣም ቆንጆ ነበር። መል ክ ነበር የሚመስለው...” ቀጠሉ። “ ሚካኤል ወርቄ አስገራሚ ሰው ነበር። ድንገት ካገኘኽው ብዙ ስለሱ እንደማስብ ንገረው….” አሉኝ። ... ከንፈራቸውን እየነከሱ ትንሽ ካቅማሙ በኋላ “ አሁንም እንድማፈቅረው ንገረው” ብለው ቆዘሙና “ታውቃለህ!” አሉ ዕንባ ያቀረረውን አይናቸውን በፈገግታቸው ለመሸፈን እየሞከሩ “ታውቃለህ! አግብቼም አላውቅ ያላገባሁትም ማንም እንደ ሚካኤል የሚሆንልኝ ስላላገኘሁ ይመስለኛል..” አሉኝ።
ሃናን አመስግኜና ተሰናብቼ ውልቅ አልኩ። አሳንሳሩን ወስጄ ወደ አንደኛ ፎቅ በመውረድ መውጫው በር ላይ እንደደረስኩ የበር ዘቡ “ አሮጊቷ ረዱህ ወይ?” ብሎ ጠየቀኝ። “ፍንጭ ሰጥተውኛል ..ቢያንስ የቤተሰብ ስማቸውን አግኝቻለሁ። ትንሽ ግዜ ወስጄ አየዋለሁ...... ቡናማውንና ከጎኑ ቀይ ማሰሪያ ያለውን የኪስ ቦርሳ ከኪሴ አውጥቼ... ዛሬ ቀኑን ሙሉ የዚህን ቦርሳ ባለቤት በመፈለግ ነው ያቃጠልኩት” አልኩት ለዘቡ። ዘቡም ቦርሳውን ሲያይ “ እንዴ! ይሄማ የአቶ ሚካኤል ወርቁ ቦርሳ ነው! በዛ በብሩህ ቀይ ማሰሪያ ክሩ የትም ቢሆን አላጣውም ፣ ይሄ ቦርሳ ሁልግዜ ይጠፋባቸዋል፡፡እኔ እንኳን በዚህ አዳራሽ ውስጥ ሶስት ግዜ ሳላገኘው እቀራለሁ? ሲል “ማናቸው አቶ ሚካኤል ወርቁ?” ብዬ ጠየቅኩት እጄ መንቀጥቀጥ ጀምሯል። “ 8ኛ ፎቅ ላይ የሚኖር ጡረተኛ ሰው ናቸው” ....... “ይሄ ቦርሳ ያለጥርጥር የአቶ ሚካኤል ወርቁ ነው ። አንዱን ቀን ሊንሸራሸሩ ወጥተው ጥለውታል ማለት ነው” አለኝ። ዘቡን አመስግኜ ወደ ነርሶች ቢሮ በሩጫ ተጣደፍኩ። ዘቡ የነገረኝን ለነርሷ ነግሬያት ወደ አሳንሳሩ ተመልሰን ገባን። አቶ ሚካኤል እንዳይተኙ ጸለይኩ። 8ኛው ፎቅ ላይ እንደደረስን “እንደመሰለኝ አሁንም በመዋያ ክፍል ውስጥ ናቸው ። ማታ ማታ ማንበብ ይወዳሉ፣ በጣም የሚወደዱ አዛውንት ናቸው” አለች ነርሷ። መብራቱ በጠፋ ብቸኛው ክፍል ውስጥ በጠረጴዛ መብራት የሚያነቡ አንድ ሰው ተቀምጠዋል። ነርሷ ወደርሳቸው ተጠግታ “ ይህ ደግ ጨዋ ሰው የእጅ ቦርሳ አግኝቶ ነበርና ድንገት የርስዎ ይሆናል ብለን
ወደ ገጽ 39 ዞሯል
ገ ጽ20
ቆይታ ከፓስተር ዶ/ር ተስፋ ወርቅነህ ጋር ... በቀላሉ አዳራሽ የሚሞላው ጎላ ጎርነን ያለው ድምፁ በራስ መተማመኑን ፍንትው አድርጎ ያሳያል። ማንነቱን ካላወቁ ወይም ቀረብ ብለው ቅንነቱን ካላዩና መንፈሳዊ አንደበቱን ካላዳመጡ ፤ አካላዊ ቋንቋውና ደረቱን ነፍቶ አካሄዱ ፓስተር ሳይሆን በድብድብ ያደገ ቦክሰኛ ነው የሚያስመስለው። ቀረብ ብለው ሲያዩት ግን በቀላሉ የሚግባቡት ተጫዋች ፣ ትሁት ፣ አንደበተ ርቱዕ ፣ ባጠቃላይ ፋሲካ ነው ፓስተር ተስፋ ። ፓስተር ተስፋ ወርቅነህ ጥርሱን ነቅሎ ያደገው ጌታ ቤት ነው። የመርካቶ አካባቢው የኳስ ሜዳ ልጅ የሰፈሩ የንግድ ተፅዕኖና የእግር ኳስ ፍቅር በቅጡ ሳይጠልፈው በልጅነቱ ለጌታ አዘንብሎ በሀገራችን ከመጀመሪያዎቹ ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች ውስጥ አንዱ ሊሆን በቃ። መርካቶ ሰባተኛ አካባቢ የነበረች አንዲት የፊንላንድ ሚሲዮን የሕይወቱ አቅጣጫ ቀያሽ ኮምፓስ ሆነችለት። ጌታን እንደግል አዳኙ አድርጎ የተቀበለባትና ፣ የትዳር አጋሩንም ያገኘው እዚችው ቤ/ክ ነውና የፓስተር ተስፋ ሕይወት በተነሳ ቁጥር እነሆ መነሳቷ አይቀሬ ሆነ። ከባለቤቱ ጋር በዚች ቤ/ክ ውስጥ የተጀመረው የፍቅር ጉዟቸው በጌታ ፍቅርም ተገምዶ ፍጹም ውሁድ አደረጋቸው። እነሆ ረጅም መንገድ ሲዘልቅ ዛሬም አዲስና ለብዙዎች ምሳሌም የሆነ ትዳር ሆነ። በጌታ ቃል አብረው አድገው፣ በጌታ ቃል ተጋብተው ፣ በጌታ ቃል ልጆች አሳድገው፣ አስተምረው ድረው ኩለው ዛሬ የልጅ ልጅ ለማየት በቅተዋል። አዎ ፓስተር ተስፋ የፍቅር ሰው ነው! አንዳንዶች ለሚስቱ ያለውን ከፍተኛ ፍቅር ሲገልጹ “በስብከቱ ውስጥ እንኳን የባለቤቱን ስም የሚያነሳበት ምክንያት አያጣም” ይሉታል። ለትምህርት ልዩ ፍቅር አለው። ዕድሜ ልኩን ትምህርት አላቋረጠም። ዶክተር ተስፋ እስኪባል ተምሯል ። ልጆቹም የአባታቸውን ፈለግ ተከትለው አንደኛው ኢንጂኔር ሌላው ሜዲካል ዶክተር ሲሆኑ የመጨረሻዋ የኮሌጅ ተማሪ ነች። በቤተሰቡ ውስጥ የተንፀባረቀው ሁሉ በሚመራው ቤ/ክ ውስጥም ይንፀባረቃል። ለቤተ ክርስቲያኑ ምዕመናን ባለው ፍቅር ፣ እንዲማሩ በማበረታት፣ እንዲያገለግሉ በማነቃቃትና በምሳሌነት ይታወቃል። የአባትነት ፣ የእረኛነትና የማስተማር ፀጋዎቹ መለያ ታርጋዎቹ ናቸው። “ጋሽ ተስፋ በራሱ የቲዎሎጂ ት/ቤት ነው” ያሉኝ ሰዎች አጋጥመውኛል። በቃ ሲፈጠር አስተማሪ ነው ። ለግማሽ ክፍለ ዘመን በጌታ ቤት ሲኖር ወንጌሉን አንግቦ ነፍሳትን ለመድረስ ሮጧል። ዛሬ በመላው ዓለም ዞረው በማስተማርና በድረ ገጽ ውስጥ ከሚታወቁት ሰባኪያን ውስጥ አንዱ ፓስተር ተስፋ ሲሆን በብዙ አካባቢ ቤ/ክ የመትከል ታሪክ ውስጥም አሻራው ተቀምጧል። ፓስተር ተስፋ የሚድ ዌስት ኮንፍራንስ መስራች እረኞች ውስጥም አንዱ ነው። የዘንድሮውን ዝግጅትም በልዩ ሁኔታ በማደራጀት ቤተ ክርስቲያኑ ለተመስጋኝነት በቅታለች። እነሆ በዚያ የኮንፍራንስ ሩጫ ውስጥ በነበረበት ሰዓት ለኛ ግዜ አገኘልንና በሕይወቱ ዙሪያ አነጋገርነው ። እነሆ አንጋፋው ወንጌላዊ ያንብቡት። የእግዚአብሔርን መልክ የሚያንፀባርቁ አድርጎ ልጆችን ማሳደግ ፣ ለልጅ ልጅ እንደ መልካም ርስት የሚወረስ በረከት ነው። ........ያኔ ህብረተስብን ፣ አገርንም የሚለውጡ ልጆች ማፍራት ይቻላል። አቶ ስዩም ገብረየስ
ለቤተክርስቲያንህ ምን ማለት ነው? መልሕቅ ፦ አገር ቤት ሄደህ ነበር የሚባል ወሬ ሰምተናል። እንዴት ነበር ያገርቤት እረፍትህና አገልግሎትህ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ቆንጆ ነበር! አገር ቤት ብሄድም አካሄዴ ግን ለአገልግሎት አልነበረም። የሄድኩት ከልጆቼና ከልጅ ልጆቼ ጋር ነው። በ1979 በስራ ምክንያት እኔና ባለቤቴ ከኢትዮጵያ ስንወጣ ሁለት ወንዶች ልጆቻችን የሶስትና የአራት ዓመት ልጆች ነበሩ። መጀመሪያ የሄድነው ኬኒያ ነው፤ እዚያ ሥራ ሰርተን እንደገና ለትምህርት ወደ አሜሪካ መጣን፡፡ መልሕቅ፡-ከሀገር የወጣችሁት በአበሻው በ1971 መሆኑ መልሕቅ፡ ነው? ፓ. ተስፋ ፡-አዎ! 1971 ነው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ አንዱን ልጄን ኮሌጅ እያለ ለጥቂት ጊዜ ሰድጄው ነበረ። አንደኛው ግን ተመልሶ ሄዶ አያውቅም። እዚህ ከመጣን በኋላ የወለድናት ሴት ልጃችን ኢትዮጵያን ተመላልሳ የማየት ዕድል ያጋጠማት ቢሆንም ሁሉንም ይዤ ነው የሄድኩት። እንዳልኩህ ቆንጆ ጊዜ ነበረን፡፡ በብዙ ያገሪቱ ክፍሎች እየተዘዋወርን ታሪካዊ ቦታዎችን ጎብኝተናል። ቤተክርስቲያን የመሄድ ዕድል ብዙ አላጋጠመንም፤ አንድ ሁለት እሁድ ሄደናል። አንደኛውን አገለገልኩበት ሌላውን ተገለገልኩበት። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ ከአገር ቤት መልስ የኮንፍረንስ ዝግጅት ውስጥ ነው እራስህን ያገኘኸው.... ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ አዎ! በቀጥታ ወደዚያ ነው የገባሁት። መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ስለኮንፍረንሱ ሆነ ስለዝግጅቱ ምን ትለናለህ? ይሄ ኮንፍረንስ ላንተ ለቤተሰብህና
መልሕቅ
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ የሚድዌስት ስብሰባ በተለይ እኔ ባለሁበት አካባቢ በጣም እንወደዋለን። የምንናፍቀውም ጉባዔ ነው። ሚድዌስት አሁን ተሳታፊ የሆኑትን አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ አፅናንቶናል ፤ አገናኝቶናል። በዕውነት የተቋቋመበት አላማ ግቡን መቷል ማለት ይቻላል፡፡ ተቀራርበናል! እንደውም ከዛም አልፈን በጋብቻም በሌላም ነገሮች ሁሉ ተሳስረናል። በዕውነት አንድ ነን! በእውነተኛ መንገድ አንድነት ይሰማናልና ለዚህ ነው የምንናፍቀው፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- እንግዲህ አሁን ወደ ዋናው ጥያቄዎቼ እየሄድኩ ነው፤ ጋሽ ተስፋ የት፣ መቼ፣ ከነማን ተወለድክ? ስንት ወንድሞችና እህቶችስ አሉህ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- (ሳቅ) ከባድ ጥያቄ አይደለም ፤ የተለመደ ጥያቄ ነው። አስፈላጊነቱን ግን አላውቅም። የእናቴን ስም መናገር አስፈላጊ ነው? መልሕቅ፡መልሕቅ፡- አዎ ምንም አይደለም…. ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ እሺ! እናቴ ወ/ሮ መቅደስ አበበ ትባላለች። አባቴ ጄኔራል ወርቅነህ ጋሻው ይባላል። ከሁለቱ ነው የተወለድኩት ሁለቱም በአሁኑ ጊዜ በህይወት የሉም፡፡ አንድ ወንድምና ሁለት እህቶች አሉኝ። ወንድሜ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል። በደርግ ዘመን ነው ይሄ የሆነው። ተመስክሮለታል ግን ጌታን አላገኘም። አሳዛኝ ነው። ሌላ ታላቅ ወንድሜ የምለው እናቴ ያሳደገችው የአጎቴ ልጅም አለ።
ገ ጽ21
ማራናታ!
መልሕቅ፡መልሕቅ፡ እስቲ እንዴት ነው አስተዳደግህ ትንሽ ብታጫውተን፤
ኃይለሥላሴ ዩኒቨርስቲ የማታ (extension program ) ገብቼ በሕዝብ አስተዳደር (public administration) በዲፕሎማ ጨረስኩ።
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ያደኩት “ኳስ ሜዳ” በሚባለው ስፍራ ነው። ለመርካቶ ቅርብ ነው። ወደ ላይም ደግሞ ራስ ሀይሉ ሜዳ ለሚባለው የጨዋታ ስፍራ ቅርብ ነው። “ኳስ ሜዳ” የሚባለውን ስሙን ያገኘው ኳስ መጫወቻም ስለነበረ ነው። ያደኩት እዚያ አካባቢ ነው።
መልሕቅ ፡፡ ከዚያስ ……?
መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የአራዳ ልጅ ነሃ / ሳቅ /
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ኖርዝ ካሮላይና (North Carolina) ነው የተማርኩት ። ከዚያ በኋላ እንደገና ለማስተርሴ ቀጥዬ Masters of Business Administration ሰርቼ ሳልጨርሰው በአገልግሎት ምክንያት ወደ ሒውስተን መጣሁኝ። በኋላም for some reason ይረዳኛል አልኩኝና ወደ Masters of Science ለወጥኩት እና በ Human Resource ማስተርሴን ሰራሁኝ። የመጨረሻውን ድግሪዬን ግን
ፓ. ተስፋ፡- ራሴን የመርካቶ ልጅ እላለሁ….. የተወለድኩት መርካቶ ባይሆንም ሁለተኛ ልደት ያገኘሁት መርካቶ ነው:: እንውልበት ፣ ሻይ ሄደን እንጠጣበት ነበር። ከርስቶስን ከማግኘቴም በፊት ሆነ ካገኘሁ በኋላ መርካቶ መዋያዬ ነበረ። እንደ እውነተኞቹ የመርካቶ ልጆች መሃል አራዳው ውስጥ ባልኖርም ያው የመርካቶ ልጅ ነኝ፡፡ አንዳንዴ አንዳንድ ሰዎችን “የመርካቶ ልጅ መሆኔን አትርሱ” እላለሁኝ……(ሳቅ) ..ቄስ ሆነን ሲያዩን ብዙዎቹ ምንም የምናውቅ አይመስላቸውም (ሳቅ)
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- አሜሪካን ከመጣን ወዲህ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን (Business Administration) የመጀመሪያ ዲግሪዬን (BA degree) ሰርቻለሁ፤ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የት ነው እሱ?
መልሕቅ፡መልሕቅ፡ የኳስ ነገር ስላነሳህ ዘለል ብዬ ልጠይቅህና ወጣት ሆነህ ኳስ ትጫወት ነበር? የማን ቲፎዞስ ነበርክ ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ እጫወት ነበር፤ የምንደግፈው ቅዱስ ጊዮርጊስ የሚባል ቡድን ነበር። ይድነቃቸው ነበረ ኃላፊው ፤ እነ ነፀረ ወልደ ስላሴ፣ አዳሙ፣ መንግስቱ ወርቁ የሚባሉ ብዙ የምናደንቃቸው ተጫዋቾች ነበሩ። እነሱን እያየን ፣ እንደ እነርሱ ለመሆን ነው የተጫወትነው። በሰፈራችን የተለያዩ የስፖርት ከለቦች ነበሩን እያፈረስንም እያቋቋምንም ልጆች ሆነን ብዙ ኳስ ተጫውተናል። ክርስቶስን ከማግኘቴ በፊት ለመድኃኒዓለም ፩ኛ ደረጃ ት/ቤቴ የሲ ቡድን ተጫዋች ነበርኩ። በኋላም ሹቲንግ ስታር ( የበራሪ ኮከብ) ቡድን ሲመሰረት ካሰባሰባቸው ተጫዋቾች መካከል ውስጥ ነበርኩበት። ካምቦሎጆ ትላልቆቹ ቡድኖች ከመጫወታቸው በፊት ለማሟሟቅ ያንን ቡድን ወክዬ የመጫወት እድል አጋጥሞኝ ደስ ብሎኝ ያውቃል ። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ አዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ ኳስ ተጫውተህ ታውቃለህ ማለት ነዋ! ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- አዎ ለአንድ ቀንም ብትሆን ተጫውቼ አውቃለሁ፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የትምህርት ሕይወትህስ ምን ይመስል ነበር?
የድል አክሊል ተስፋ ነው፤ እዚህ አገር ከመጣን ወዲህ ወርቅነህ የሚለውን ስም ወስዶ ተስፋ የመካከለኛ ስም ሆኗል፡፡ ወደ አገር ስንመለስ ወርቅነህን ትቆርጣላችሁ ተስፋ ይፀናል ብያቸው ነበር እንግዲህ እስካሁን አልተመለስንም። (ሳቅ) ሁለተኛው ልጄ ብሩህ ተስፋ ፣ ሶስተኛዋ ከንዓን ተስፋ ትባላለች። መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የትዳር ጓደኛህ ባገልግሎት ውስጥ ያላት ዕርዳታ ወይም አስተዋጾዖ ምን ይመስላል? በዚህ አጋጣሚ የሌሎችን አገልጋዮች የትዳር ጓደኞች ምን አይነት መሆን አለባቸው ትላለህ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ሁሉንም ነች! ሁሉ ነገር ! ያለሷ ማገልገልም ምንም ነገር ከባድ ነው።….ለኔ መቼም “ክርስቶስ ህይወቴ ነው ሞትም ጥቅሜ ነው” እንዳለው ጳውሎስ ከርስቶስ ሁሉም ነገሬ ነው፡፡ ከክርስቶስ ቀጥሎ በህይወቴ ቦታ ያላት ፣ ያለሷ በእውነት ኑሮ ምንም የማይመስለኝ፣ በአገልግሎቴም ጉልበቴ የሆነች፣ ከጌታ ቀጥሎ ያለችኝ እሷ ብቻ ነች፡፡ ያለሷ ማገልገል አልችልም፡፡ ማንኛውም አገልጋይ ሚስት ሊኖረው ይገባል፡፡ በቤቱ እንከን ያለው፣ ወይም ችግር ያለው፣ አንገት የሚያስደፋ ታሪክ ያለው፣ እግዚአብሔር የሚወደው አይነት ትዳር የሌለው ሰው በእውነት ቤተክርስቲያንን ደስተኛ ሆኖ ማገልገል ይችላል
2011 ኮንፍራንስ ላይ ከባለቤቱ ጋር የሰራሁት በመንፈሳዊ ነገር ነው፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- መቼ ነው ያገኘኽው? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ይመስለኛል ከአስር - አስራሁለት ዓመት በፊት ነው በቢብሊካል ጥናት (Biblical Studies) የዶክትሬት ድግሪ (PHD) ያገኘሁት ። መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የትዳር ጓደኛህን እንዴት አገኘሃት? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ጌታ ቤት ነው ያገኘኋት። ድሮ ፊንላንድ ሚሲዮን የሚባል መርካቶ ሰባተኛ አካባቢ ያለ ቤተክርስቲያን ነበር ፡፡ እዚያ ነው ያገኘኋት። በዕድሜ ከአምስት እስከ ስድስት ዓመት እበልጣታለሁ። እሷ ደግሞ ትናንሽ ልጆች ሆነው ጌታን በማግኘት የእሁድ ትምህርት ከሚሄዱት መካከል አንዷ ነበረች፡፡ አስራ ሁለት አመቷ ላይ በደንብ ጌታ ማን እንደሆነ ታውቃለች። ለድነት የሚሆነውን እውቀትና ትምህርት ሁሉ አግኝታለች፡፡ .... እዛው አደግን፣ ተፈቃቀድን በጌታ እንዋደድ ነበረ የበለጠ ደግሞ በትዳር ተሳሰብን…. መልሕቅ፡መልሕቅ፡ መቼ ተጋባችሁ?
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ እድሜ ልኬን ሰማር ነው የኖርኩት (ሳቅ ) ያንን ሁሉ መቁጠሩ ያስቸግራል። ከቄስ ትምህርት ቤት ወጥቼ ፈረንሳይ ትምህርት ቤት ገባሁ። አባቴ በሆነ ምክንያት ፈረንሳይኛ እንድማር ፈልጎ ነበረ። በኋላ ደግሞ ኃሳቡን ቀየረና አረብኛ መማር አለብህ አለኝ። ዑመር ሰመተር የሚባል ትምህርትቤት ገብቼ አረብኛ እስከ አራተኛ ክፍል ድረስ ተምሬያለሁ። በኋላም አቋርጬ አንደኛ ደረጃም ሁለተኛ ደርጃም የጨረስኩት መድኃኒዓለም ትምህርት ቤት ነው፡፡
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- የተጋባነው 1974 February 10 ነው፡፡ በአበሻ የካቲት 1966 አብዮቱ ሊፈነዳ አንድ ሳምንት ሲቀረው
ከዚያ በኋላ ሥራ ስለጀመርኩኝ ቀዳማዊ
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ውሂብ ዘውዴ ትባላለች፤ ልጆቼ ትልቁ
መልሕቅ፡መልሕቅ፡ የሚገርም ነው (ሳቅ) ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ምክንያቱም በኛ ሰርግ ሳምንት ድንጋይ ውርወራው ተጀመረ፡፡ በቤንዚኑ፣ በታክሲዎች ችግር፣ ምክንያት የቀረውን ታሪክ ታውቁታላችሁ። አንድ ሳምንት ብቆይ ኖሮ ሰርጌ የተበላሸ ይሆን ነበር፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ባለቤትህ ማን ትባላለች? ልጆቸህስ?
የሠርጋቸው ቀን ከ37 ዓመት በፊት የካቲት 3 1966
ብዬ አላስብም፡፡ ካገቡ በኋላ ጌታን ያገኙና የሚያገለግሉ ሰዎች ጉዳይ የሚታየው በሌላ ነው። ክርስቲያን ሆነው የሚያገቡ ሰዎች ግን አስቀድመው ይሄን ሁሉ ማጣራት፤ ትክክለኛውን ምርጫ ማድረግ ይገባቸዋል። ድሮ አንድ ፈረንጅ ሲናገሩ “ዲያቢሎስ እንኳን አማች አድርገውት ቀርቶ እንዲሁም አልተቻለም.....” ብለው ነበር (ሳቅ በሳቅ) መልሕቅ፡መልሕቅ፡- እንዴት ነው ጌታን ያገኘኸው? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ጌታን ያገኘሁት ፊንላንድ ሚሲዮን
ውስጥ ነው። መርካቶ። ልጆች ሆነን
“ዲያቢሎስ እንኳን አማች አድርገውት ቀርቶ እንዲሁም አልተቻለም.....” አልተቻለም.....” ከፓስተር ተስፋ ትዝታ
ገ ጽ22
ሚሽን ሄደን ከለር ስንቀባና አንዳንድ የመፀሀፍ ቅዱስ ታሪኮች ስንሰማ ደስ ይለን ነበር። ካደግኩ በኋላ ደግሞ አንዳንዴ ከልጆች ጋራ መርካቶ
ሙሽሮቹ !
ወንጌል እንሰማ ነበር። ታዲያ አንድ ቀን አንዲት ሲስተር ኤልቪት የምትባል ፊንላንዳዊት ድንግላዊት ሚሺነሪ (አሁን በህይወት ትኑር አትኑር አላውቅም) ከዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ፪ ስለ እነዚያ ስድስት ጋኖች ታስተምር ነበር። ያለስራ ደጅ በተቀመጡ፣ ምንም ጥቅም ባልነበራቸው ጋኖች ውስጥ ክርስቶስ ውሃውን ወደ ወይን ለውጦ ብዙዎችን ሰዎች እንዴት እንዳረካባትና እነኛን ጥቅመ ቢስ ጋኖችን ጠቃሚ መገልገያ ያደረገው ክርስቶስ ምን ያህል የሰዎችንም ህይወት እንደሚቀይር በእንባ ታስተምር ነበር። በመልዕክቱ ውስጥ የወንጌል ጥሪም ታደርግ ስለነበረ ህይወቴን ሙሉ በሙሉ ለጌታ የሰጠሁት የዚያን ጊዜ ነው፡፡ የክርስቶስ ፍቅር ውስጤ የኖረውና ጌታን ያገኘሁት ፤ በአበሻ በ1955 አካባቢ ነው። ምንም ዘመኑ ቢረዝምም በሀምሳ ስድስት መጠመቄን ግን በትክክል አስታውሳለሁ፡፡ መልሕቅ፦ የአገልገሎት ህይወትህ እንዴት ተጀመረ? ወደ ሙሉ ጊዜ አገልግሎትስ እንዴት ተሸጋገርክ?
ልጆቻቸው
የልጅ ልጆቻቸው ( መንትዮች)
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ የሙሉ ግዜ አገልግሎት ሲባል ስራ ትቶ መቶ በመቶ ለኑሮ የሚያስፈልግህን ሁሉ በቤ/ክ ላይ አድርጎ ማገልገል ከሆነ በቅርብ የዛሬ 12 ዓመት ገደማ ነው የጀመርኩት። አሜሪካን ከመጣሁ በኋላ አሁን ላለሁበት ቤ/ክ ፓስተር ሆኜ ስራውን የጀመርነው ጃንዋሪ 1984 ነው። ከዚያን ግዜ ጀምሮ እስከ 1999 ድረስ ሌላ ስራ በተጓዳኝ እየሰራሁ ነው ያገለገልኩት። አገልግሎት የግድ ስራ ትተህ መሆን አለበት የሚል አይመስለኝም። አገልግሎት ሕይወት ነው። በዕለት ኑሮህ፣ ባንደበትህ፣ በስራህ ቦታ፣ በድርጊትህ፣ በሁሉ ነገርህ የእግዚአብሔርን መንግስት ማስፋፋት ነው። እኔም እንደዚያ ሳደርግ ነው የኖርኩት። የቤ/ክ አገልግሎቴ እያደገ፣ እየሰፋ ፣ እየበዛ መጥቶ ስራዬን እንድተው እስኪያስገድደኝ ድረስ አንድ መንፈሳዊ ድጋፍ ሰጪ ድርጅት ( Para church ) ውስጥ በዳይሬክተርነት አመራር እሰጥ ነበር። ስራውም ገቢውም ጥሩ ነበር። በኋላ ግን ሁለቱን አጣምሬ መስራት የምችልበት ሁኔታ ውስጥ አልነበርኩም። በቃ ስራው ትልቅም ባይሆን ለኔ ተለቀብኝ። በዛብኝ። ስለዚህም ግልጋሎቴን ወደዚህኛው ብቻ አደረግኩ። መልሕቅ፡መልሕቅ፡- “ሥራም እየሰራህ የሙሉ ጊዜ አገልጋይ ልትሆን ትችላለህ” እያልከን ነው? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ አዎ ጳውሎስ እንደሱ ነዋ!
መልሕቅ
ጳውሎስ ለኑሮው ድንኳን እየሰፋ (“ማንም ላይ ሳልከብድ” ይላል) ያገለግል ነበር፡፡ ምንም ስህተት የለውም፤ ሰው ሁሉ ይሁን ማለቴ አይደለም። ስለዚህ አሁን ነው ሙሉ በሙሉ ሌላ ሥራ ሳይኖረኝ ቤተክርስቲያን ላይ ያተኮርኩት። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ በየትኞቹ የዓለም አካባቢዎችና ከተሞች ላይ አገልግለሃል? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ከአውስትራሊያ በስተቀር ያልሄድኩበት አህጉር የለም። ሁሉም ቦታ ሄጄ አገልግያለሁ፡፡ እንዳጋጣሚ ግን እዚያ ሄጄ አላውቅም፡፡ በአህጉር ደረጃ ማለቴ
ሰብስበን በራሳችን ቋንቋ እንድናገለግል የእግዚአብሔር ፈቃድ ሆነ ። መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ታስረህ ታውቃለህ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ አዎ መልሕቅ፡መልሕቅ፡ መቼ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ኢትዮጵያ ውስጥ በኃይለሥላሴ ዘመን ስደት እስሩ መርካቶ ውስጥ በኛ ነው የጀመረው። በሳምንቱ አራት ኪሎ ያሉትን ደግሞ ሰበሰቡና አሰሩዋቸው። እንደገና ወደ ሾላ አካባቢ ጎጃም መንገድ ላይ፤ ከዚያም ደግሞ አሁንም መርካቶ ውሰጥ ከኛ ወረድ ብሎ አዲስ ከተማ ውስጥ የነበሩትን ፤ ባጠቃላይ ሶስት አራት ቦታ የነበርነውን አገልጋዮች ነው የኃይለሥላሴ አስተዳደር ወስዶ እስር ቤት የከተተን። ከዚያም ሌሎችን ከርቸሌ ሳይቀር ጨመረ። እኔ ከርቸሌ አልወረድኩኝም ፤ ግን መርካቶ አራተኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ ያለውን ችግር ሁሉ ቀምሻለሁ፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ባንተ በዘመንህ የነበረውን የክርስቲያኖች ኅብረት፣ የእምነት ጥንካሬ፤ አምልኳችሁን፣ መዝሙራችሁን..........እኔ ባለፈው ኮንፍራንስ ላይ“ዳዊታዊ አምልኮ” እያልክ ስታስተምር ሰምቻለሁ አስቲ የነበረውን ሁኔታ ትንሽ አካፍለን
ፓስተር ተስፋና ቤተሰቡ ነው። በከተሞችም ብንሄድ በአውሮፓ ውስጥ ብዙ ከተሞች አገልግያለሁ። አፍሪካ ውስጥ የነበርኩበት ኬኒያ እኖር እንደነበር ነግሬያችኋለሁ ሥራዬም መንፈሳዊ ድርጅት ውስጥ ስለነበር ያው አገልግሎት ነው። መልሕቅ፡- ባገር ቤት በጨለማው የስደት ዘመን ያንተ የህይወት ዕጣህ ምን ላይ ነበር የጣለህ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ በስደቱ ወቅት ማለትም በደርግ ዘመን በክርስቲያንነቴ በክርስቲያን ላይ የደረሰው ችግር ሁሉ አጋጥሞኛል። በቤተክርስቲያን መሪነቴም ችግር ገጥሞኛል። የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ናዝሬት ላይ ሲቋቋም የመጀመሪያው ፀኃፊ ነበርኩ። የካቶሊክን ቤተክርስቲያን ጨምረን በኋላም የኦርቶዶክስም ቤ/ክ አባልነት ጠይቃ ገብታ ሁሉንም ያጠቃለለ የኢትዮጵያ አብያተክርስቲያናት ህብረት የሚባል ኅብረት አቋቁመን ነበር። ቄስ ጉዲና ቱምሳ የሚባሉ ደርግ የገደላቸው የእግዚአብሔር ሰው ነበሩ የሚመሩት። (ታሪካቸውም ሬሳቸውም ወጥቶ በክብር ያረፈ የእግዚአብሔር ሰው ናቸው..) እኔ የዚያ ህብረት አስተባባሪ (coordinator) ነበርኩ። መካነየሱስ ህንፃ ላይ ቢሮ ሰጥተውን እስከወጣሁበት ጊዜ ድረስ በሙሉ ጊዜ ሥራ እንሰራ ነበር። ከዚህ የተነሳ በጊዜው የነበረው ችግር ሁሉ ፍርሃቱም ሌላውም ነገር ሁሉ አጋጥሞኛል። ግን እግዚአብሔር ታማኝ ነው! ቅድም እንዳልኩህ ነው መመሪያዬ:: “ክርስቶስ ህይወት ነው፤ ሞትም ቢሆን ጥቅም ነው”። ግን እንድንሞት የእግዚአብሔር ፈቃድ አልነበረም። ወደ ውጭ እንድንወጣና በውጩው አለም የተበተነውን ህዝባችንን
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ መቼም እግዚአብሔርን አምልከነዋል። በደንብ ከልብ ! የዚያን ጊዜ ሳስተምርም እንደተናገርኩት አምልኮ በእውነት መሆን አለበት። ሰዎች የሚሰጡን አስተያየት ሌላ ነው፡፡ እግዚአብሔር ግን እንዲመለክ የሚፈልገው በእውነትና በመንፈስ ነው ። ዝርዝር ውስጥ ብዙ አልገባም ያ መሆኑ ነው ጥሩ። እግዚአብሔርን ከልብ፣ ከእውነት፣ በእውነት እንደቃሉ አምልከናል። ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው አምልኮ ከሚሲዮናውያን የመጣ ስለነበረ ልብ ይነቀንቃል እንጂ በአሁኑ ጊዜ እንደሚታየው ዓይነት ሰውነትን መነቅነቅ የሚጨምር አልነበረም፡፡ ውዝዋዜ የለም። ሌሎችን ነገሮች ሁሉ አያጠቃልልም፡፡ የሚያደርጉም ሲኖሩ ያንን እንዳያደርጉ ይመከሩም ፣ ይታገዱም ነበር። ካገልግሎትም እንኳን የተወገዱ አሉ፡፡ ያየነውና እኛም እራሳችን ያደረግነው ይሄንኑ ነው፡፡ ግን ሲገባንና ስንደርስበት አሁን ለየት ያለ ነው። አሁን ያለው ሁናቴ ሁሉ የዛን ጊዜ ቢደረግ ኖሮ ይመስለኛል ከቤተክርስቲያን እንዲወጡና እንዲባረሩ ሊደረግ ይችል ነበረ፡፡ ስላልደረስንበት ማለት ነው፡፡ እና ያንን ነው የጠቀስኩት ያሁኑ መልካም ነው የደረስንበት የአምልኮው ዘይቤው መንገዱ ደህና ነው፡፡ ዳዊታዊ ነው ግን ማንኛውም ነገር ከልብ ካልሆነ እንደቃሉ ካልሆነ እንደው ስላሸበሸብን ብቻ እግዚአብሔርን ደስ አለው ማለት አይደለም፡፡ የአምልኮ ትልቁ መለኪያ ይሄ ነው፡፡ እኛ ደስ ሲለን ሳይሆን እርሱ ደስ ሲለው ነው፡፡
የክርስቶስ ፍቅር ውስጤ የኖረውና ጌታን ያገኘሁት በአበሻ በ1955 አካባቢ ነው። ፓስተር ተስፋ ወርቅነህ
ገ ጽ23
ማራናታ!
ፓ. ተስፋ፡-ያኔ ተስፋ፡ ድሮ በልጅነት ጎረምሳ ሆኜ፤ አንድ ሰው ስሜን በውሸት ቢያጠፋ፤ እልኸኛ ስለነበርኩ እውነቱን ለማውጣት እሰከመጨረሻው ድረስ ፓ. ተስፋ፡-አላውቅም። ተስፋ፡ ይቅርታ ምናልባት እሄድ ነበር፡፡ ይህ ከሚሆን ብሞት ይሻለኝ ነበር። እንዴት? የሚል ጥያቄ ሊኖር ይችላል..እኔ አሁን ግን ማንም ተነስቶ ምንም ቢለኝ ግድ እንጃ እንዳልኳችሁ ምናልባት ባለቤቴ የለኝም፡፡ በጌታ እየቆየሁ ስመጣ ያገኘሁት ምክንያቴ ነች። ልጆቼ ምክንያት ይሆናሉ። እግዚአብሔር ቅድም እንዳልኩህ ለውጥ ይሄ ነው፡፡ እሱ ጠበቃ ቢሆን ፣ እሱ ለእስጢፋኖስ ሶስት ሺ ድንጋይ ፣ ለጴጥሮስ ቢቆም ይሻላል፡፡ ሶስት ሺ ነፍሳት ነው የሰጠው። እኔ እግዚአብሔር ብዙዎች ባለፉበት ዓይነት ተስፋ በሚያሰቆርጥ ሁኔታ ውስጥ እንዳልፍ አድርጎኝ አያውቅም፡፡ እንደውም አሞላቆ ነው ያኖረኝ። ድካሜን ስለሚያውቅ መሆን አለበት። ጌታን እወደዋለሁ። አገለግለዋለሁ። ፕሮብሌሞች ያጋጥሙኛል፤ አላጋንናቸውም! ቸግር ማለት ቸግር ነው፡፡ መፍትሄ ማግኘት አለብን። ማለቴ ማንም ሰው ከሆነ ችግር አለው ። ችግር ሰው የመሆን ምልክት ነው፡፡ እነሱ አይገጥሙኝም ማለቴ አይደለም፡፡ ተስፋ መቁረጥ ማለት... በቃ ምንም ይሄንን አላልፈውም ። እግዚአብሔር አይረዳኝም። ትቶኛል። በቃኝ ዓይነት ሁናቴ ላይ እኔ ደርሼ አላውቅም፡፡ እኔ እንጃ እኔን በኮረኮንቹ መንገድ ሳይሆን በለስላሳው መንገድ የወሰደኝ ሰለሚያውቅ ነው እሱ። በልጅነቴ ጌታን ስላገኘሁ አሱም ከባለቤቱና እረድቶኛል፡፡ ብዙዎቹን ችግሮች አላውቃቸውም፡፡ ባለቤቴም ጋር ከልጅ ልጆቻቸው ጋር የተገናኘሁት በልጅነቴ ነው፡፡ ትዳር የጀመርኩት በሃያ አምስት ዓመቴ ነው፡፡ በትዳር እሷም እኔን ፣ እኔም እሷን ብቻ ነው መልሕቅ፡መልሕቅ፡ ከፍቶህ ያውቃል? የምናውቀው፡፡ ምርጫም ሳደርግ ለጋብቻ ብዬ በጌታ ቤትም እያለሁ ያሰብኳትም ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ አዎ….አዎ ግን አስፈላጊ አይደለም የመረጥኩትም አብሬ የተጓዝኩትም ማንም አላነሳቸውም፡፡ እግዚአብሔር ቤት ውስጥ ያሉ ሰው የለም እሷው ነች። ስለዚህ ችግሮችን የሚከፉ ነገሮች አጋጥመውኛል። ኢትዮጵያም አላየሁም ማለቴ ነው፡፡ ሌሎች ያጋጠማቸው ውስጥ እዚህም ግን ያ ችግሬ አይደለም… ማለቴ ብዙ ችግሮች እንዳሉ አውቃለሁ። ቅድም ያሳዘኑኝ ነገሮች ማለቴ ነው፡፡ እንዳልኩህ እግዚአብሔር ማንነቴን መልሕቅ፡- እንዴት ነው ይቅርታ የማድረግ ስለሚያውቅ ሊሆን ይችላል በእነኛ መንገዶች መልሕቅ፡ባሕሪህ? አላሳለፈኝም፡፡ ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ምርጫ የለህም፤ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- መፅሀፎች ጽፈሃል? መልሕቅ፡መልሕቅ፡- በጌታ ስትኖር ተስፋ ቆርጠህ ታውቃለህ?
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- አዎን ጽፌያለሁ፤
መልሕቅ፡መልሕቅ፡ ምንም ችግር የለብህም?
ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ምንም ምርጫ የለህም፡፡ ማንም የአባቴ ገዳይ ወይም የእናቴ ገዳይ እንኳን ቢሆን ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ለጥቂት ሰዎች የተሰራጩና (እናቴን እወዳታለሁኝ ያሳደገችኝ ነች) ይቅር ልለው በአብዛኛው ለሕዝብ ያልደረሱ ጥቂት ግድ ነው። አንድ ሰው አጥፍቶ ይቅርታ ሲጠይቅ መጻሕፍት አሉኝ። በትናንሽ መጽሔት መልክና በብትንም ዓይነት ብዙ ጽሁፎችን ይቅር ማለት ካልቻልን በጣም ከባድ ህይወት ጽፌያለሁ፡፡ ለአንዳንድ ችግሮች እንደምላሽም ውስጥ እንገኛለን፡፡ እንደውም ሳንጠየቅ ልንሰጠው ሆነው የጻፍኳቸው አሉ፡፡ በብዛት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ ……በርግጥ ብዙ ነገር ስላልተሰራጩ አሁን ብጠቅሳቸው በኋላ ያደረሰብህን አንድን ሰው መልሶ ማመን ቃለ አባይ ተብዬ እጠየቅባቸዋለሁ፡፡ ይከብዳል። ያ ይቅር ያልከው ሰው ራሱ earn ታትመው በአለም ዙሪያ የተሰራጩትን ሊያደርገው የሚገባው ነው፡፡ “ሁሌ ይቅርታ ሰጪ “መንፈሳዊ እድገት” እና “ክብርት ነበርክ ወይ?” ብትለኝ አልነበርኩም። እንዳልኩህ ቤተክርስቲያን” የሚባሉትን መጥቀሱ በጣም ለሀቅ ለእውነት የመቆም ነገር ስለነበረኝ። ይበቃል። በብዙ አርዕስት ላይ ብዙ የጻፍኳቸው አሉ ፣ እንግዲህ ጊዜያቸውን ተስፋዬ ጋቢሶ አንዴ “እውነት በራሷ ብቻዋን ጠብቀው ይወጡ ይሆናል፡፡ አጥንት ነች” አለ፤ “ፍቅር በራሷ ደግሞ ብቻዋን መልሕቅ፡መልሕቅ፡- የትኞቹ ባህሪዎች ናቸው እውነት ከሌላት ቁርበት ነች” አለ፤ ስለዚህ ድሮ የሚያስቸግሩህ? በተለይ ጎረምሳ በነበርኩበት ግዜ ክርስቲያን ነኝ ግን የእውነት ነገር በኃይል ያጠቃኝ ስለነበረ ወደ መጥፎ ነገሮች ውስጥ ወስዶኝ ሌላውንም ቧጥጬ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ስንት መፅሃፎች?
፣ ተቧጥጬም አውቃለሁ፡፡ ከነኩኝ ለእውነት፣ ለምን ? በሚል መንገድ ችግሮች ነበረብኝ። አሁን ግን ችግሬም አይደለም። ደስ ይለኛል ማለቴ ግን አይደለም (ሳቅ) እኔ እንጃ ደስ የሚለው ማንንም አላውቅም፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ጌታን ስታገኘው መጀመሪያ የምትጠይቀው ነገር ምንድነው? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ለምን እንደወደደኝ? እኔ እንጃ አይገባኝም። ለእኔ ሲል የሆነውን ሁሉ ለምን እንደሆነ ነው የምጠይቀው፤ እሱ ይገርመኛል። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ በህይወትህ ዘመን ብዙ አሳልፈሃል ። ህይወትህን ድጋሚ መኖር ብትችል ደግመህ የማታደርገው ነገር ምንድነው? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ እንደክርስቲያን ወይስ………? መልሕቅ፡መልሕቅ፡- እንደክርስቲያን… ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ምንም! ምንም የለም። አሻሽዬ የማደርጋቸው ግን አሉኝ። አሻሽዬ የማደርጋቸው ስል ካሁኑ የበለጠ፤ አቅም ባጣሁበት የበለጠ አቅም ኖሮኝ እንዳደርጋቸው፤ እውቀት ባጣሁበት የበለጠ በማወቅ እንዳደርጋቸው የምፈልጋቸው ነገሮች ይኖሩኝ ነበር። አይቻልም ። የሚቻልም ነገርም አይደለም። እንደዚያ ላለው ጥያቄ መልስ መስጠት አስቸጋሪ ነው፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ጌታ እንደአላዓዛር ሁለት ሰዎች ከሞት የማስነሳት መብት ቢሰጥህ ከዘመዶችህ ውጪ እነዚያ ሁለት ሰዎች እነማን ይሆናሉ ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- ከዘመዶቼ ውጪ? (ሳቅ) ከባድ ጥያቄ ነው፤ ከዘመዶቼ ውጭ ማንን ላስብ ጌታን ሳያገኝ የሞተ አንድ ጓደኛ አለኝ። አብረን ነው ያደግነው። ብዙ ስለወንጌል ነገርኩት። ፈቃደኛ አልሆነም ። መለያየት የግዴታ አስፈላጊ ስለነበር ተለያየን። ተለያይተን ጌታን ሳያውቅ ሄደ። ስው ክርስቶስን ሳያገኝ ሞተ ማለት የሚሄድበትን አውቃለሁ። ሰው ያለክርስቶስ ያለተስፋ ሲቀር ያሳዝነኛል። በቀረው እንግዲህ፤ በጣም ብዙ ሰው አለ፤ ጌታን ሳያገኝ የሞተ እገሌ ልልህ አልችልም አይሆንም እንጂ ሁሉም እድል ቢያገኝ … መልሕቅ፡መልሕቅ ያ ሰው ግን ልብህ ውስጥ ያለ ሰው ነው.. ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ አዎ እሱ አንድ ጓደኛዬ ነው ... መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ማን ይባላል? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡ ዘረ ሰናይ ይባላል። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ በዘንድሮው የ2011 ሚድዌስት ኮንፍራንስ አዘጋጅ ቤ/ክ ፓስተርነትህ ለኮንፍረንሱ ተካፋዮች የምታስተላልፈው መልዕክት ካለ? ፓ. ተስፋ፡ተስፋ፡- አዎ ከዚህ በፊትም ተናገሬዋለሁኝ። ምናልባት ካሁን በኋላም ብዙ ጊዜ እናገረው ይሆናል። ሚድ ዌስት የፓስተሮች ህብረት አይደለም። የአብያተ ክርስቲያናት ህብረት እንጂ፡፡ ሰዎች ይለዋወጣሉ ፣ ይቀያየራሉ፣ ያልፋሉ ከሚድዌስት አንድ ሰው መውጣት ይችላል። ምናልባት ፓስፊክ ኮስት፤ ወይም ደግሞ አትላንቲክ ኮስት መሄድ ይችል ይሆናል። በሚድዌስት መስመር ላይ ያሉ ቤተክርስቲያኖች ግን ሁልጊዜ ቋሚ ነዋሪዎች ስለሆኑ ፤ በዚህ በሚድዌስት ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ የኛ ነው ብለው እንዲይዙት፤ አላማውንም ተግባሩንም ራዕይ አደርገው እንዲተገብሩት እመኛለሁኝ፡፡ መልሕቅ፡- ጋሽ ተስፋ ስለሰጠኸን ቃለ ምልልስ በመፅሔቱ ስም እጅግ አድርጌ አመሰግንሃለሁ! ጌታ ይባርክህ!
ገ ጽ24
667 ደቂቃዎች ከገጽ 16 የዞረ መልሕቅ፦ ስለ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያንሽ ትንሽ ብታጫውቺን? ማነው ፓስተርሽ...... ሒሩት፡ሒሩት፡-ፓስተራችን ሳሚ ይባላል። እኔ ብዙ ግዜ በዙረቱ ምክንያትና አሜሪካም ሄጄ ስለምቆይ ቤ/ክ ብዙ አልሄድም። ካለሁም እግዚአብሄር ይመስገን ቤተ ክርስቲያኔ ቃል ተካፍዬ የምዘምርም ከሆነ ዘምሬ
ሒሩት በዝማሬ ላይ
ወደቤቴ እመጣለሁ። ቅድም መጀመሪያ ስናገር በነገሬ ሁሉ ፍቅርን ነው የምፈልገው። ፍቅር በጣም እንደውሃ ነው የሚጠማኝ። ማለት ፍቅር ማለት የክርስቶስ ባሪያዎች ሆነን ሁላችን እንድንፋቀር ጌታም ይወዳል። ኢየሱስ ማለት ፍቅር እኮ ነው። ፍቅር ነውና የምፈልገው ብዙ ነገር ውስጥ ጠለቅ ብዬ አልገባም። እናም አገልግዪ ባሉኝ ሰዓት አገለግላለሁ...... መልሕቅ፦ በቋሚነት አንድ ቤ/ክ አትሄጂም ማለት ነው? ሒሩት፦ ቤተ ክርስቲያኔማ እዛ ነው። (መሠረተ ክርስቶስ ማለቷ ነው) ያውቃሉ እነሱም በብዛት ለአገልግሎት እንደምወጣ። መልሕቅ፦ ከሰው ፀባዮች የማይመቹሽ የትኞቹ ናቸው? አንዳንዱ ጉረኛነት አንዳንዱ ምቀኝነት ይላል አንቺስ? ሒሩት፦ ሒሩት ሳቅ ዕውነት ነው! ጉራ ለሰው ልጅ አስፈላጊ አይደለም። ያው ብዙ ጉረኞች ይኖራሉ ....ግን እኔ አላውቅም እንደዚህ ዓይነቱን ነገር ሳይ አልወድም። ደስም አይለኝም ። የፈለገው ነገር ሀብታም ይሁን የፈለገው ነገር ይኑረው ጉራ ጥሩ አይደለም። ማለት ወደ ውርደት ሁሉ ይጥላል ጉራ ። እኔ የምወደው ራሱን ለጌታ ዝቅ የሚያደርግ ሰው ነው። ትዕቢተኛ ሰው ደስ አይለኝም። እጠላዋለሁ ሳይሆን ለራሴ ደስ አይለኝም። ብዙ ሰዎች አሉ ከበድ ያሉ ቃላቶች የሚናገሩ። ለምን አስፈለገ? አያስፈልግም እንደዚህ ዓይነቱ። ባህርዬ እንደዚህ ነው። ኩርፊያ አልወድም። እንግዲህ ውስጤን ንገሪኝ ካልከኝ ቁጣ አልወድም። አላግባብ ንግግር መወርወር አያስፈልግም። የኔ ባህርዬ ከሁሉ ጋር መፋቀር ነው ከጎረቤቱም ከምኑም። ቢያስቀይሙኝም ደግነቱ ቶሎ እረሳዋለሁ። በዚያ ሰው ባዝንም እረሳዋለሁ። እንደዛ ነው የኔ ባህርይ። መልሕቅ፦ በምድርሽ ላይ ምን እንዲሆን ትሺያለሽ? ሒሩት፦ የኔ ምኞት በፊት በልቤ ይሞላ የነበረው ቅድም ስንነጋገር ጌታ ይሄን ሰዓት ቢሰጥሽ ምን ታደርጊያለሽ እንዳልከው ጌታን ለማያውቁ ሰዎች ኮንፍራንስ ሆኖ ዘማሪዎች ሁሉ ተጠርተው ሰባኪዎች በብዛት ተጠርተው ሕዝቡን በሙሉ ጋብዘን በሙዚቃም በልዩ ልዩ ስራ ውስጥ ያሉትን በሙሉ ሰብስበን ጌታን እንዲያውቁ ማድረግ ነው መልሕቅ
ምኞቴ ። በብዛት ሰዎች ጌታን እንዲያገኙ ነው የልቤ ሸክም ። መልሕቅ፦ አንቺ በዓለም በነበርሽበት ወቅት በጣም ታዋቂና ተወዳጅ ሰው ነበርሽ። እናም የኛ ኅብረተሰብ በልዩነት ዕምነቱ ይሄን ያህል ነውና ጌታን በመቀበልሽ ምክንያት ኃይማኖትሽን የቀየርሽ ተብለሽ በምትሄጅበት ቦታ፣ በገበያ ቦታ ፣ በመንገድ ላይ ያጋጠመሽ ችግር ነበር? ሒሩት፦ አንድ ግዜ አገልግዬ መስክሬ ስወጣ ብዙ ወጣቶች እደጅ ይጠብቁኝ ነበር። የጌታ መንፈስ ግን በቦታው ላይ “አንበሳ አለ አስሬዋለሁ” እያለ ይናገር ነበር። የሚደንቀኝ ነገር ጌታ እኔን ሰው ብሎ “አንበሳ አለ አስሬዋለሁ” የሚል መልዕክት ለኔ ይተላለፋል ብዬ አልጠበቅኩም ነበር። ለሌሎች ለታላላቅ ሰዎች እንጂ። እንዴት ከዚህ ሁሉ መሀል ጌታ ሆይ ብዬ ነበር የማስበው። ይገርማል! በኋላ እዚያ የጠሩን ሰዎች ለካስ ተጨንቀዋል። “ቆይ ትውጣ ... እንደዚህ እናረጋለን ሲሉ ሰምተው። በመኪና መጥተው የወሰዱኝ እነሱ ስለነበሩ “እንዴ እኔ እኮ መሄድ አለብኝ ውሰዱኝ” እላቸዋለሁ። “ቆይ እስቲ ትንሽ ቆይ...መኪናዋ እንትን ሆና ነው” ይላሉ ተጨንቀው። በኋላ ፀለዩና አልገባኝም እኔ በመሀላችቸው እየተራመድኩ ስወጣ...የተናደዱብኝ በግራና በቀኝ ቆመዋል። ብዛታቸው ምን ብዬ ልንገራችሁ። እጃቸውን አጣምረው ጠበቁኝ። በስመአብ የስድቡ ነገር አይወራ “ጌታ ይባርካችሁ! እወዳችኋለሁ!” እያልኩ ወጣሁ። እግዚአብሄርን ግን አንድ ቀን እነዚህን ልጆች አገናኘን እንዳልኩት አደረገ። ጌታን ተቀብለው እነሱም አገልጋይ ሆነው አገኘኋቸው። ደስ የሚል ታሪክ ነው! ሌላ ብዙ አይደለም አልፎ አልፎ ነው እንዲህ ዓይነቱ ነገር የሚከሰተው። ሰዎች ይነጋገሩበታል ግማሾቹ “ወደ አምላኳ ነው የሄደችው” ግማሾቹ ደግሞ “እንዴት እንዲህ ታደርጋለች?” እያሉ። አሁን ግን ነገሩ ሁሉ መልካም ሆኗል። እነዛ ወጣቶች ገና እንደጀመርኩ ነበረ ኃይለኛ ነገር ያደረጉት እግዚአብሄር ግን ሰላምን አውርዶልኛል። ጌታ ሞገስ ሆኖኛል። ከመኪናው ጋር አብረው እየሮጡ “ ሌባ! ሌባ! ” ይሉ ነበር። ጌታ ይባርካቸው። እግዚአብሄር ባርኳቸዋል። እና ያ ሁሉ አሁን ቀርቷል። እግዚአብሔር ይመስገን አንድ ሰሞን የነበረ ነው። ቤቴም ላይ ድንጋይ ውርወራ ነበረ። ግን ይህ ሊሆን ግድ ነው። አንድ ሰው ሲናገር “እንደዚህ ዓይነት ፈተና ውስጥ ማለፍ ከሌለ ከሰይጣን ጋር ተስማምተናል ማለት ነው” አለ መፈተን አለብን። ዕውነት ነው! ጌታ ኢየሱስ በምድር በነበረ ግዜ ደልቶት አይደለም የኖረው። ተርቦ ተጠምቶ ...እዛች በለስጋ እንኳን ሲሄድ “አንዳች ቢያጣባት ረገማት” ይላል የእግዚአብሄር ቃል። መልሕቅ፦ ከመዝሙሮችሽ መካከል ብዙ ቦታ ለመዘመር የምትወጃቸው የትኞቹን መዝሙሮችሽን ነው? ሒሩት፦ ብዙ አሉ በጣም የምወዳቸው እግዚአብሔር የሰጠኝ መዝሙሮች። “አንተ ለኔ ተዋጊ” የምትለዋን መዝሙሬን እወዳታለሁ። ሌላም ብዙ ብዙ መዝሙሮች ከሕይወቴ የተነሳ የምወዳቸው አሉ። በመድረክ ላይ ሳገለግል ከኦዲየንሱና ከሁኔታዎች የተነሳ አያቸዋለሁ፤ ማን የትኛውን መዝሙር እንደሚወድ። አንዳንድ ግዜ ደግሞ እኔ የምወደውን ሕዝቡ ላይወደው ይችላል።
እንደዚህ ዓይነትም አጋጣሚ አለ። መልሕቅ፦ ከመዝሙሮችሽ በስተጀርባ በግጥምና በዜማ የረዱሽ ሰዎች ካሉ? ሒሩት፦ አዎ! አንድ በጣም የምወዳት እህቴ አለች እሷ ትረዳኛለች። ይሄ ማለት እንዲህ ነው እያልን ተሰብስበን እናርመዋለን። አብረን እንማከራለን። እግዚአብሔር ፀጋ ሰጥቷታል። መልሕቅ፦ መልሕቅ ማን ትባላለች? ሒሩት፦ ብዙዬ ትባላለች። መልሕቅ፦ የከለር ምርጫሽን ብትነግሪን? ሒሩት፦ በብዛት ነጭ ቀለም በጣም እወዳለሁ። ብጫም ደስ ይለኛል። ሶስተኛ ደግሞ አረንጓዴ፤ ለምን እንደሆን አላውቅም እነዚህን ከለሮች ናቸው ምርጫዎቼ። መልሕቅ፦ ከሀገራችን ምግቦችስ የቱን ትወጃለሽ? ሒሩት፦ /ከሐገራችን ምግቦች እያለች ማስብ ጀመረችና ሳቅ/ በተለይ ከበግ ስጋ ምግቦች ዱለት በጣም እወዳለሁ፣ ቅቅል፣ ምላስ ፣ (ሳቅ ) ጥብስ ነገር የመሳሰሉትን እወዳለሁ። ያው ደግሞ ማንም እንደሚያውቀው ዶሮ ወጥ ! መልሕቅ፦ ከቲያትርና ከፊልም ጋር ግንኙነትሽ ምን ይመስላል?
ለሐጢያታችን ዕዳ......
ሒሩት ፦ ብዙም ግንኙነት የለኝም። መልሕቅ፦ መጽሐፍ ማንበብስ ትወጃለሽ? ሒሩት፦ ብዙ መጽሐፍ አንባቢ ነኝ አልልም፤ ርዕሱን አይቼ የሚማርከኝ ከሆነ አነበዋለሁ። መልሕቅ፦ ከጌታ ነገር ውጭ መዝናኛሽ ምንድነው? ሒሩት፦ ከጌታ ነገር ውጭ ብዙም የሚያዝናናኝ ነገር የለም። በነገራችን ላይ ምስክርነት በጣም እወዳለሁ። እሱ በጣም ያዝናናኛል። ከዚያ ውስጥ ለኔ ለልቤ የሚቀርልኝ ነገር ስላለ ከወንድሞቼጋ ከእህቶቼጋ ቁጭ ብዬ ቃል መከፋፈልን በጣም ነው የምወደው። ፀሎት እወዳለሁ በጣም! መልሕቅ፦ በሕይወትሽ ያስደነቀሽ ሰው ማነው? ለምን? ሒሩት፦ አሁን በቅርቡ ያስደነቀኝ በጌታ የሆነ ሰው ጀሹዋ ( T. B. Joshua) ነው። በፊት ቤንሂንን ( Benny hinn ) አደንቀው ነበር። ጀሹዋን ግን እጅግ በጣም አደንቀዋለሁ። እግዚአብሔር የሰጠው ፀጋ እጅግ የሚያስቀና ነው። በጣም! …ሁልግዜ በዲሽ እናየዋለንና ስጦታው እያደገ እሱ ደግሞ ለሌሎች እያወረሰ ነው ያለው ስጦታውን። በጣም አደንቀዋለሁ! እግዚአብሔር የሰጠው ፀጋ እጅግ ታላቅ ነው።
ገ ጽ25
ማራናታ!
መልሕቅ፦ እንደው በመንገድ ላይ ስትሄጂ ወይም ታክሲ ውስጥ ድሮ የተጫወትሻቸውን ዘፈኖች ስትሰሚ የሚሰማሽ ነገር ምንድነው? ሒሩት፦ ምንም አይሰማኝም እኔ። ትኩረት ሰጥቼ አላዳምጠውም ። መልሕቅ፦ ኢትዮጵያን አይድል የሚባል ፕሮግራም ላይ የድሮዋን ሒሩትን (አንቺን) ለመምሰል የሚመኙና የሚወዳደሩ ወጣቶች አሉና በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ይሰማሻል? ሒሩት፦ እንደነገርኩህ ምንም አይሰማኝም ያለፈ ነገር ስለሆነ። /የታዘብኩት ነገር ስለ ዘፋኝነት ዘመኗ ብዙም መናገር እንደማትፈልግ ነው/ መልሕቅ፦ አንቺ ጌታን አግኝተሽ አለም ከንቱ መሆኗን ተረድተሽ ነው ያለሽው እነኚህ ልጆች ደግሞ ገና አንቺን ለመምሰል የሚመኙና የሚጥሩ ናቸው። ምንድነው ስለነዚህ ልጆች የምታስቢው? ሒሩት፦ እንግዲህ እግዚአብሔር በግዜውና በሰዓቱ ነው ሁሉን ማድረግ የሚወደውና ጌታ በግዜው ምናልባት ይጠራቸው ይሆናል። እኔ እሱን ሳይሆን በጣም ሕጻናቶች በሙዚቃ ዓለም ውስጥ ያሉትን ሳያቸው በቃ በጣም አዝናለሁ። ከዚህ በፊት እንደዚህ ብዬ ስናገር የሰሙኝ ሰዎች እሷን ለዚህ ደረጃ አብቅቷት የነበረው ሙዚቃ ሲሆን በሙዚቃ ሌላው እንዳይታወቅ እንዲህ ትላለች ይላሉ። ለሱ ብዬ አይደለም እኔ። ማለቴ አሁን የጌታ ነገር ውስጤ በጣም ከገባ በኋላ ነገሮች ሁሉ ቁልጭ ብለው ስለሚታዩኝ ስለነዛ ብላቴኖች አዝናለሁ። ምንም የሚያቁት ነገር የሌለ ሕፃናቶች ናቸውና ። መልሕቅ፦ የሐገር መሪዎች ፊት የመቅረብ ዕድል አጋጥሞሽ ነበር? ሒሩት፦ ነገስታቶች ፊት ማለት ነው? መልሕቅ፦ አዎ ለምሳሌ ግርማዊ ጃንሆይ ፊት… ሒሩት፦ አዎ! ግርማዊ ጃንሆይጋ ለልደታቸው ግዜ ቀርቤ አንድ የወርቅ አምባርና ብሮች ተሰጥቶኛል። በሌላ ግዜ ደግሞ አንድ የጦር ልምምድ ቦታ ሄደው ነበርና ታላቅ ድንኳን ተተክሏል። መሬቱ ሁሉ ምንጣፍ ሆኖ ብዙ ጄኔራሎች ባሉበት ምግብ እንድናቀርብ ታዘዝን፤ ከቦዮቹ ተጨማሪ ማለት ነው። ጾም ነበር ቀኑ እሳችቸውጋ ለማድረስ ለኔ የተሰጠኝ አሳ ነበር ። ግራና ቀኝ በጣም የበዙ ጄኔራሎች በተቀመጡበት ውስጥ ማለፍ በጣም ያስፈራ ነበር። ጃንሆይንም ቀና ብዬ አላየኋቸውም። “ ይዘሽ የመጣሽው ምንድነው?” ብለው ሲጠይቁኝ አሳ እንደማለት ከድንጋጤ የተነሳ “fish ነው ግርማዊ ሆይ!” አልኳቸው። /ሳቅ / ሳቅ ብለው ዝም አሉ። በተፈጥሮዬ ልጅ ሆኜም ድንጉጥ ስለነበርኩ ያ ነገር እያደገ መጥቶ ነው እንደዛ የሆንኩት ። ከዚያ በኋላ ገብቼ ለቦዮቹ ነገርኳቸው። በጣም ሳቁ “ fish ነው አልሻቸው?” እያሉ። ወርቁን ከዚያ በኋላ ነው የሸለሙኝ። አለቃችን ከቢሯቸው አስጠርተውኝ “ከጓደኞችሽ ጋራ ለሽልማት ጃንሆይ ፊት ትቀርቢያለሽና ርስት ይሰጠኝ፣ እንዲህ ይሁንልኝ ፣ እንዲህ ይደረግልኝ እንዳትይ” አሉኝ። “ኧረ እኔ አይወጣኝም አልኩና” ገባሁ። ጃንሆይ “ከኢትዮጵያ ውጭ ወጥተሽ ታውቂያለሽ?” ብለው ጠየቁኝና... በጣም የገረመኝ ነገር በራሳቸው እጅ በፖስታው ላይ ስሜን በትክክል በቁም ጽህፈት ጻፉ። “ሒሩት በቀለ” ብለው። “ያውቁኛል እንዴ?” አልኩና በልቤ እጅ ነስቼ ወደ ቤቴ ገባሁ። አንድግዜ ደግሞ አሳምነው ገብረወልድ ይመስለኛል
ኢንተርቪው ሲጠይቃቸው “ሕይወት እንደሸክላ እንዳለችው ዘፋኟ” ብለው ሲመልሱለት ያንን ሙዚቃ የተጫወትኩት እኔ ነኝና ለካስ ያውቁኛል አልኩ። መልሕቅ፦ መልሕቅ አንቺና ሙሉቀን መለሰ ሕይወታችሁ በ
ዘማሪዋ አለምም በጌታም ተገናኝቷልና ያ በአንድ ዓይነት ሕይወት ውስጥ የማለፋችሁ ታሪክ ግንኙነታችሁን የተለየ አድርጎታል? ሒሩት፦ የተለየ ነገር እንኳን የለም። ያው እሱም ከኔጋ ፖሊስ ሙዚቀኛ ውስጥ ይሰራ ነበረ። በጣም ትንሽ ወጣት ነበር። በኋላ የምሽት ክለብ ግዮን ይሁን ሌላ ቦታ ገባ። ይመስለኛል እዛ እንደሆነ ነው ጌታን ያገኘው። አንድ ጓደኛው ነው የመሰከረለት ። እንደነገረኝ ይዘፍንና እንደገና ሄዶ በጨረቃ ላይ ትንሿን መጽሐፍ ቅዱስ ያነባል። ከዚያ በኋላ አሜሪካ ሄዶ ፈጽሞ ወደጌታ ገባ ። ዲሲ ስሄድ አግኝቼዋለሁ። በስልክም አገኘዋለሁ። አሁን ጥሩ አገልጋይ ሆኗል። መልሕቅ፦ ባሁን ሰዓት መተዳደሪያሽ ምንድነው? በምንድነው የምትኖሪው? ሒሩት፦ እግዚአብሔር ይመስገን! ገቢዬን የሚያመጣው ጌታ ነው። እኔ ማገልገል ብቻ ነው። ሁለተኛ ደግሞ ልጆቼን አስነስቶልኛል። ልጆቼን እግዚአብሔር ይባርካቸው! መቼም የእናት ወግ የሚያሳዩ ልጆች ናቸው። እነሱ ናቸው በድንቅ ሁኔታ የያዙኝ። አባቴ አስነስቷቸዋል። ለኔ እንዳደረጉት እነሱ ደግሞ በልጆቻቸው እንዲደሰቱ እግዚአብሔር እንዲያደርግልኝ እፀልያለሁ። የጡረታም አለኝ ። እግዚአብሔር ይመስገን! ድሮ ከነበርኩበት አሁን ያለሁበት ይበልጣል። አሁንም አንድ ጥያቄ ቀረኝ ልትል ነው? ሳቅ በሳቅ መልሕቅ፡ - አልልም አልልም! ሳቅ .......አሁን ያንቺ ነው የምትጨምሪው ነገር ካለ? ሒሩት፦ አንድ ምስክርነት ልጨምርልህ። ጌታ ያደረገልኝ አስደናቂ ነገር አለ። ወደኋላ ልመልስህና ጌታን ካገኘሁ አንድ ስድስት ወር አካባቢ የሆነ ነገር ነው። እኔ ጌታን ሳገኝ በሆዴ ጽንስ ነበር። ትንሽ ከቆየሁ በኋላ ምግብ እንቢ ሲለኝ ድሮ ጽንስ በምይዝበት ግዜ የምወስደው ክኒን ነበር እሱን ከአንድ ፋርማሲ ገዝቼ ስወስድ አልተስማማኝም ። ምንድነው ብዬ ዶክተሬጋ ሄድኩኝ። “አሁን አንቺ በጣም ደከም ደከም እያልሽ ስለሆነ ሌላ ግዜ መጥተሽ በደንብ እመረምርሻለሁ” አለኝ። እሺ ብዬ ተመልሼ ቤቴ ገባሁ። ይደክመኛል። ምግብ አልበላም። አንድ ቀን ሰባት ወሬ ላይ ህጻኗ ሆዴ
ውስጥ ከሚገባው በላይ ተንደፋደፈች ። “እንዴ! እንደዚህ ዓይነት ነገር አላውቅም ምንድነው እሱ ” ብዬ ዝም አልኩ። ከዛች ደቂቃ በኋላ መጫወት የለም ልጅቷ ። ደነገጥኩ በቃ ። ስተኛ አብራኝ የምትተኛ ይመስለኛል። “ እንዴ ምንንድነው ይሄ ነገር እስቲ እዚህ ሀኪምጋ ልሂድ አልኩና ሄድኩ። እሱ ህፃኗ ሆዴ ውስጥ እንደሞተች አውቋል ። እግዚአብሔር ሰርጀሪ አርጎ እንዳያወጣ እጁን ሲይዝልኝ “አንድ ነገር ሲሰማሽ ቶሎ ባስቸኳይ ወደኔጋ ትመጫለሽ አለኝ። ያኔ እንደዛሬ ብዙ ስፔሻሊስት አልነበረም። ዶ/ር ሶኮሎቭ ይባል ነበር ያ ሀኪሜ። ከድካም በስተቀር ምንም ነገር አይሰማኝም። ስሄድ “ሌላ ግዜ ተመለሺ ደህና ነው” ይለኛል። “ምንደነው ነገሩ?” ....አሁን ሞታ ቢሆን ኖሮ ያወጣው ነበር ይሄ ዶክተር” እያልኩ ግራ እንደተጋባሁ ቆየሁ። ልክ በሁለት ወሩ ነፍስ እንዳለው ህጻን ምጥ መጣ። የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ! ምጥ ሲመጣ “ ልክ ነው! ልጅቷ አልሞተችም ማለት ነው” አልኩኝ። ሆስፒታል ሄድኩኝ። ዶክተሩ ተጠርቶ መጣ። ማታ ልወልድ ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ ነው የገባሁት። ሁለት መርፌ ወጋኝና ትተኛ አለ ተኛሁ። እዚህ ሀገር የልጆች አልጋ ያስቀምጣሉ ። የኔን አውጥተውታል። “ምን ማለት ነው? ለምን አልጋውን አወጡት? ” አልኩኝ። አንድ ልጅ አለች አጠገቤ “እስቲ ሌሎች ክፍል ሂጂና የልጆች አልጋ እንዳለ እዪ” ብዬ ላኳት። “ሁሉምጋ አለ አንቺጋ ብቻ ነው የሌለው አለችኝ” “እንግዲህ በኋላ ሊያመጡ ይሆናል” ብዬ ጌታ አዕምሮዬን ጠብቆታልና ዝም አልኩኝ። በኋላ ምጥ መጣ በኃይል ፤ ሰርጀሪ ሳልሆን በትክክል ምጡ ነፍስ እንዳለው ሕጻን ወጣ። አያስደንቅም? ዶክተሩ ህፃኗን አሳየኝ ሴት ልጅ ነበረች። የምታምር ፀጉሯ ግንባሯ ላይ ድፍት ያለ። ይኼውልሽ ልጅቷ ከሞተች ሁለት ወሯ ነው እንዳትደነግጪ ብዬ ነው አለኝ። እግዚአብሔር ይመስገን! ብታሳዝነኝም ምንም ማድረግ አልችልም እግዚአብሔር ነፍሴን አተረፋት።እግዚአብሔር እንደዚህ ያለ አስደናቂ ነገር በኔ ሕይወት ሰርቷል። በሌሎችም ሰርቷል ወደፊትም ይሰራል! ሁለት ወር ሙሉ ሙት ጽንስ ስሸከም ደሜም ሊመረዝ ይገባ ነበር። ከውስጥ አንዳንድ ነገሮችም ሊበላሹ ይገባ ነበር። እኔን ግን “ነጻ ነሽ!” አለኝ ዶክተሩ። መልሕቅ፦ ዘማሪ ሒሩት ስለሰጠሽን ቃለ ምልልስ በጌታ ስም እናመሰግናለን!
ይሄ ቃለ መጠይቅ እንዲሳካ የረዱንን እህት ሒሩት ብርሃኑን ፣ ወንድም ዘረሰናይ ብርሃኔን፣ አቶ ጌቱ ምንሽርንና የሰሊሆም ሬስቶራንት ባለቤቶችን ከልብ እናመሰግናለን።
ገ ጽ26
ሚድ ዌስቶች ጌታን የምናመልክበት ስፍራ አጭር ታሪክ ፎልስ ክሪክ የኮንፍራንስ ማዕከል ጥቅጥቅ ያለ ደንና ያልለማ ጭንጫ የመሬት ገጽ የተላበሰውን የአርቡክል ጋራ ለተመለከተ ተራራ ወጭዎችን ለመገዳደር ሊኖረው ከሚችለው ተስህቦ ውጪ ፋይዳ ቢስ ተደርጎ የሚታይ አካባቢ ነበር። የጌታ ራዕይ ጥሪ ግን በአዕምሮ ለማሰብ የማይቻለውን ቁልጭ አድርጎ ለማሳየት አስቻለ። የሰው ልጅ ሊከናወን ይችላል ብሎ ከሚያስበውና ከሚገምተው ባሻገር ፣ በጌታ ዕይታና ፈቃድ ሊሆን የማይችል አንድም ነገር የለም። ለዚህም ነው ደኑንና ወጣ ገባውን እንዲሁም የውሃ ቁሬውን ለህዝቦች መሰባሰቢያና አመቺ የአምልኮ ቦታነት የመቀየር የጌታ ጥሪ ለ ጄ ቢ ራውንድስ እና ዳብልዩ ዲ ሙረር (J. B. Rounds and W. D. Moorer) ወለል ብሎ የታያቸው። ራውንድስ እና ሙረር ለመጀመሪያ ግዜ የቦታውን ይዞታ የተመለከቱት በ 1917 ዓ/ም ዴቪስ ከተማ ፀጉር ማስተካከያ ቤት ግድግዳ ላይ ከተለጠፈ ፎቶግራፍ ላይ ነበር። እነሱም ለዚህ 160 ሄክታር መሬት በቅጽበት ልባቸው ተማርኮ J.B. rounds & W.D moorer ለባፕቲስት ክርስቲያን ወጣቶች ኅብረት ዓመታዊ የበጋ መገናኛነት ተመኙት። የኦክላሆማ መንግስትም ቋሚ ካምፕ እንዲሆን ፍላጎቱም ፈቃዱም ሆነ። በዕምነት ጢም ብለው የተሞሉት እነዚህ ሁለት የእግዚአብሄር ሰዎች ያንን ራዕይ መከተል ጀመሩ። በራዕያቸው ላይ የነበራቸው ዕምነት እንደ ብረት የጠነከረ ነበርና አንጡራ ሃብታቸውን በማፍሰስ የንብረቱን ባለቤትነት አረጋገጡ። ከዚያም ቦታውን ለማመቻቸትና የራዕያቸውን ፍሬ ለማየት እጃቸውን በንብረቱ ላይ አዋሉ። ራውንድስና ልጁ ብቻ ከፕራይስ ፎልስ እስከ የጉባኤ ማዕከሉ ድረስ ያለውን ግማሽ ማይል መንገድ ጠርገው አበጁ። ታሪክ ፀሃፊዎች እንደጠቆሙት ራዕዩ ካልገባቸውና ካልተዋጠላቸው ሰዎች ከባድ ተቃውሞ ተነሳ። ወላጆች ልጆቻቸውን ወደዚህ አስቸጋሪ ስፍራ የመላኩ ጠቀሜታ ጎልቶ አልታይ አላቸው፡፡ ይህም ተቃውሞ ከጌታ በተቀበሉት ራዕይ ላይ ምንም ጥርጣሬ ያልነበራቸው ሙረርና ራውንድስ ራዕያቸውን በትክክል የመተርጎም ችሎታቸው ላይ ልባቸው ጥያቄ አጫረባቸው። ስለዚህም ከጌታ ማረጋገጫ ፈለጉ። በዚህ ጉዳይ ላይ ታሪክ ፀሃፊዎች ዋነኛውን ክስተት የመዘገቡት በ1917 ዓ.ም ጁላይ ወር መጨረሻ ላይ ሙረር ከራውንድስ ጋር በመሆን ቦታውን በጎበኙበት ወቅት ነበር። ሁለቱ ለካምፕነት ምርጥ ቦታ ነው ብለው የወሰኑትን የባዛርድን ተራራ አብረው በመውጣት ላይ እያሉ ውይይታቸው ያተኮረው ስፍራውን ለካምፕነት የማይስማማ በሚያደርጉት እንከኖቹ ላይ ነበር። በተራራው ጫፍ ላይ ሲደርሱ ቦታውን ለጌታ አሳልፈው ሰጡ። ሙረር በጉዳዩ ላይ የጌታን ፈቃድ ለማወቅና የእሱንም ትዕዛዝ ለመፈጸም ስላላቸው ፈቃደኝነት ፀለየ። ራውንድስ አንድ ነገር በእርግጠኝነት እንደሚያውቅ ይሰማው ነበር። የፀሎት ቃላቶቹም ኃላፊነት ካደረበት ልቡ ውስጥ በጥንቃቄ የተመረጡ ነበሩ። ፀሎቱም “ አባት ሆይ ! ለዚህ የጉባኤ ስፍራ ብዙ ጥረናል፣ለፍተናል። ሁለታችንም በእጅጉ ወደነዋል። ነገር ግን ያንተን ፈቃድ ሳናይ ቀርተንም ይሆናል። የኦክላሆማ ባፕቲስት ጉባኤውን በፎልስ ክሪክ እንዲያደርግ ፈቃድህ መሆኑን እናውቅ ዘንድ አባት ሆይ አንድ ሰው አንተን በመቀበል ሲድን አሳየን…… “ የሚል ነበር ። አንድ ቀዳሚ ሪፖርት እንዳመለከተው 273 ሰው ለመጀመሪያው ጉባኤ ተመዝግበዋል። በመጨረሻውም እሁድ ራውንድስ በአቅራቢያ ከሚገኝ እርሻ የመጡ ፒየር እና ቦኒ ብሩቤከር የሚባሉ ሰዎች አጠመቀ። እንደ ፀሎቱ አንድ ሳይሆን ሁለት ሰዎች ጌታን ተቀበሉ። የፀሎት ጥያቄው ማረጋገጫ እስካሁኗ ግዜ ድረስ የቀጠለ ሲሆን በ 2006 ዓ/ም በጋ ላይ ብቻ 44002 ሰዎች በፎልስ ክሪክ ካምፕ የተሳተፉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 5243 ቱ ጌታን እንደ ግል አዳኛቸው ተቀብለው ውሳኔያቸውን በሕዝብ ፊት አሳውቀዋል። ከ1917 ዓ/ም ጀምሮ 1.8 ሚሊዮን የሚሆኑ ሕዝቦች ቦታውን የረገጡ ሲሆን 200.000 የሚደርሱ የካምፑ ተሳታፊዎች ሕይወትን የሚቀይር ውሳኔ በማድረግ ጌታን አግኝተዋል። በምድራችን ላይ ከሚገኙ ቦታዎች ሁሉ ብዛት ያላቸው ሚሽነሪዎች የሕይወት ዘመን ግልጋሎት የሰጡበትን ጥሪ የተቀበሉት ከዚህ ከፎልስ ክሪክ ማዕከል ነው። የወጣቶችን ካምፕ በአርቡክል ተራሮች ላይ የመመስረት ሕልም ምክንያታዊና የሚያከትምም ነበር። ምንም እንኳን በወቅቱ ካምቱን መመስረቱ ፈታኝ ቢሆንም “ ጥሪው “ ካምፕ የመመስረት ጉዳይ ብቻ አልነበረም። በፍጹም! ጥሪው በክብር የመለወጥ ተራራ ላይ 19-20 ለደቀመዝሙሮቹ እንደተሰጠው “ ማቴ 28 19E A A E E E A E E E E ” እንደሚለው መሪ ቃል ነው። ይህም መሪ ቃል የፎልስ ክሪክ ዋነኛ ራዕይና የጉልበት ምንጩ ሆኖ ቀጥሏል። Re: hp://www.fallscreekok.org/ መልሕቅ
ከፎልስ ክሪክ ኮንፍራንስ ማዕከል ዌብ ሳይት የተተረጎመ
ገ ጽ27
ማራናታ!
እነሆ 17 ዓመታት ያስቆጠረው የሚድዌስት አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ በዚህ በተቀደሰ ስፍራ መካሄድ ከጀመረ ፰ ዓመታት ሆኖታል። ወደዚህ ወደ ፎልስ ክሪክ ኮንፍራንስ ማዕከል ቀጭኑን ጠመዝማዛ መንገድ ተከትላችሁ ዳገቱን ስትነዱ የደኑ ጸጥታ የመኪናችሁን ድምጽ ያጎላዋል። በጋራው ላይ ብዙም ሰው ሰራሽ የሆነ ነገር ስለሌለና ጌታ ያበጃት ተፈጥሮ ብቻ ስለሆነች የሆነ የመንፈስ ዕርካታና ሰላም ውስጣችሁን ይሞላዋል። ሰው ከሰው ሰራሽ ነገሮች ርቆ ፈጣሪ ወደሰራት ተፈጥሮ በተጠጋ ቁጥር ስለምን የህሊና ሰላም ያገኛል? በማለት አሁን ከራሳችሁ ጋር መነጋገር ትጀምራላችሁ ። “ እኔ ማነኝ? ለምን ተፈጠርኩ?” ወዘተ ዓይነት የፍልስፍና ጥያቄ አዕምሯችሁ ይጭራል ። ወደ ጋራው አናት ስትቃረቡ ባሻገር ከሚታየው ኮረብታ ላይ ትልቅ መስቀል ታዩና ለፍቅር የተከፈለው ታላቅ ወሮታ ፊታችሁ ድቅን ብሎ ዕንባችሁን ይጠራዋል። ወደ ማዕከሉ ስትደርሱ የዚች ዓለም ውጣ ውረድ ፣ ለኑሮ ሩጫው ይረሳና የተረጋጋ ያምልኮና የፀሎት ሕይወት ይወርሳችኋል። በኮንፍራንሱ ወቅት ፍቅር ይነግሳል። ሕብረት ያብባል። ሰላም አካባቢያችሁን ይሞላዋል። የዋህነት፣ ቅንነትና ደግነት፣ ክፋትና ምቀኝነትን አለማዊነትን ደምስሰው ይደምቃሉ። ሃዘን በደስታ ፍርሃት በተስፋ ይዋጣል። በአካባቢው የምታዩት የጉባኤው ተካፋይ ሁሉ የቅርብ ዘመዳችሁ ይመስላችኋል። አዳራሹን የሞላው የኮንፍራንሱ ተሳታፊ አጠገቡ ሌላ ሰው የሌለ ያህል አምላኩን በነፃነት ያመልካል። አንድ አምላክ ብቻ ይመለካል። ግራና ቀኙ ፣ ባዳራሹ የሚታየው ነገር ሁሉ የመንፈስ ቅዱስን በስፍራው መገኘት አፍ አውጥቶ ይናገራል። በቃ እንዲህ ነው ቆይታችሁ። ለጌታ እጅግ የምትቀርቡበት 72 ሰዓታት። ይሄ በየዓመቱ ያየነውና የምንመሰክረው ነገር ነው። ዘንድሮም እንደ ከርሞው ጌታ ከኛ ጋር ነበር። ከኦገስት 11 እስከ 14 2011 እ ኤ አ የተካሄደውን የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ ያደራጀችልን የሒውስተኗ የኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ኅብረት ቤ/ክ ነበረች። ከፍትፍቱ ፊቱ እንዲሉ በተለያዩ ቀለሞች አሸብርቆ ተሳታፊውን የጠበቀው የምዝጋባው /የእንግዳ መቀበያው/ ዴስክ ወትሮ የነበረውን መጨናነቅ አስወግዶ ተሳታፊው የመመገቢያውን የእጅ አልቦ ምልክትና የማረፊያ ቦታውን በግዜ እንዲያገኝ በማድረግ ስልጡን አቀባበል አድርጎለታል። በምግብ ቤቱ ውስጥ በሒውስተኖች የቀለጠፈ አገልግሎት ረክተናል። የኮንፍራንሳችን አንዱ መለያ የሆኑት የሻትል አገልግሎት የሚሰጡትን ጎልፍ መኪናዎች ዘንድሮ አየሩ ቀዝቀዝ ያለ ስለነበር ፈላጊያቸው ከወትሮው ቀነስ ያለ ቢሆንም ወዲያ ወዲህ በማመላለስ ተጠምደው አይተናቸዋል።
Campers arriving in 1917
የ2011 ሚድ ዌስት ኮንፍራንስ ተካፋዮች እንደደረሱ
የ2011 ኮንፍራንስ መሪ ቃል “ማራናታ!” 1ኛ ቆሮንቶስ 16:22 የጉባኤው ተካፋዮችን እጅግ ያነቃቃ ሲሆን ከዝግጅቱ መሪ ከዶክተር ዕውነት ጋሻውበዛ ባገኘነው መረጃ መሰረት በዚህ መሪ ቃል ስር 110 ሕፃናትና 467 አዋቂዎች በድምሩ 577 ሰዎች ጉባኤውን ተካፍለዋል። በዚህ በኮንፍራንስ ቆይታችን ወቅት በዶ/ር መንግስቱ ለማ የመድረክ መሪነት 8 የስብከትና 3 የዓውደ ጥናት አገልግሎት በ7 ፓስተሮችና በ4 ወንድሞች ተሰጥቷል። ምዕመኑን ጠይቀን እንደተረዳነው በተሰጡት ትምህርቶች እጅግ መንፈሳዊ ዕርካታ እንደተገኘባቸው ሲሆን “ማራናታ ለአማኞች ሁሉም ነገር ነው” ፤ “ጌታ እንደሚመጣ ብንጠብቅ ከኃጢያት እንታቀብ ነበር”፤ “ለዚህ ዓለም ነገር አንጨነቅም ነበር” ፤ “ማራናታ ባይኖር ተስፋ ቢሶች ነበርን” በማለት የገለጹልን ወገኖች አጋጥመውናል። የትምህርቶቹን የሲዲና የዲቪዲ ቅጂ ከሒውስተንና ዳላስ ቤ/ክ ድረ ገጽ ላይ ማግኘት እንደሚቻልም ተነግሮናል።
የመጀመሪያዎቹ ካምፐ ካምፐኞች የመመዝገቢያ ቦታ
የ 2011 ሚድ ዌስት ኮንፍራንስ ምዝገባ
የአምልኮ ፕሮግራሙን የሒውስተን ቤ/ክ መዘምራን፣ ከሀገር ቤት ተጋባዥ ዘማሪ ዮሴፍ በቀለ፣ የዳላሱ ዳንኤል ዓምደ ሚካኤል ፣ የሒውስተኗ አዜብ ኃይሉና የሴንት ልዩሱ ዶክተር ለዓለም ጥላሁን በማስመለክ አገልግለዋል። በዚህ በዘንድሮው ከማለዳ ፀሎት እስከ ምሽት የሚዘልቀው ፕሮግራም ብዙዎችን ያነቃቃና የባረከ እንደነበርና የወጣቶቹና የህፃናቱም
ፕሮግራም እንዲሁ የተዋጣለት እንደነበር የዓይን ምስክር ሆነናል። መልሕቅ የ2011 ሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናትን ኮንፍራንስን ለመዘገብ ቀደም ያለ ዓላማና ዝግጅት ባይኖራትም የመጨረሻው ሰዓታት ላይ በመቀላቀል የኮንፍራንሱን ገጽታ ለማሳየት ጥረት አድርጋለች። የጉባኤው ተካፋዮች የሆኑትን ህጻናትን ፣ ወጣቶችና አዋቂዎችን በማነጋገር የጉባኤውን ገጽታ ለማሳየትና፣ የቤተሰባቸውን ሁኔታ ፣ የመጡበትን ከተማና ቤ/ክ ፣ የትምህርት ደረጃቸውን፣ የሀገር ቤት መኖሪያቸውን፣ ስለጉባኤው ያላቸውን አስተያየት ቃለ ምልልስ መልስ በማስፈር ለወደፊቱ ለሚደረጉ ዕቅዶች ትንሽዬ ፍንጭ ሰጪ መረጃ ለማግኘት በቅታለች። እነሆ የሚቀጥሉት 7 ገጾች ከሚድ ዌስቱ መንፈሳዊ ጉባኤ ጋር በተያያዘ የተፃፉ መጠይቆችን ስናቀርብ በሁሉም ወገኖች ውስጥ ለመንፈሳዊ ሕይወታችን የሚሆን ጠቃሚ ነገር ታገኛላችሁ ብለን እንገምታለን። መልካም ንባብ። ወደ ገጽ 28 ዞሯል
ገ ጽ28
ቆይታ ከ2011 ኮንፍራንስ የዝግጅት አስተባባሪዎች ሰብሳቢ ጋር
መልሕቅ ፤- በመጀመሪያ ማን ልበል ስምህን? ዶ/ር እውነት፦ ስሜ ዶክተር እውነት ጋሻው በዛ እባላለሁ ። ከሂውስተን! መልሕቅ ፤- በቤተክርስቲያንህ ውስጥ ምንድነው አገልግሎትህ? ዶ/ር እውነት ፤- በተለያዩ አገልግሎቶች አገለግላለሁ።
ባስተባባሪነት መረጠ።፡ አስተባባሪዎች ደግሞ በየስራችን የስራ ክፍፍል በኃላፊነት ወስደን ወደ አስራ ሶስት የሚሆኑ ንዑስ ኮሚቴዎችን በማቋቋም አስፈላጊውን ዝግጅት ስናደርግ ቆይተናል፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- በስርህ ምን ያህል ሰው አሰማርተሃል? ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ በስሬ ወደ ሃያ አምስት ሰዎችን አሰማርቻለሁ። መልሕቅ - ምንያህል ሰዎች በዘንድሮው ኮነፍራንስ ተካፍለዋል፤ ወንዶቹና ሴቶቹ ምን ያህል ናቸው? ዝርዝሩ ብትሰጠን፡፡ ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ በዚህ ስብሰባ ላይ በርካታ ሰዎችን አግኝተናል። የጌታን በረከት የሚካፈሉበት፣ በመንፈሳዊ ነገራቸው የሚጠቀሙበት፣ ደግሞ በአመት ውስጥ ካለው ሩጫም የሚያርፉበት እና የእረፍት የሱባኤም ጊዜ ነው የሚሆነው። ባጠቃላይ ባሁኑ ሰዓት ወደ ስድስት መቶ የሚሆኑ ተሳታፊዎች አሉ ፎልስ ክሪክ ውስጥ። ( ዝርዝሩን ሰጠን) መልሕቅ - እሺ፤ በብዛት ከየትኛው ቤተክርስቲያን የመጡ ናቸው ማለት ነው?
ዶ/ር ዕውነት ጋሻውበዛ የሚሸነሪዎችን ስራ ማስተባበርና ለስራውም የሚያስፈልገውን ገንዘብ ለማሰባሰብ የሚደረገውን ጥረት አስተባብራለሁ። በዚህ ስብሰባ ደግሞ የአስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሆኜ የማገለግል ነኝ። ኮሚቴው ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ነው ያለው በዛ ላይ በኃላፊነት ሁሉንም የምረዳ ነኝ፡፡ ዶ/ር እውነት ፡- ባለትዳርና የሁለት ወንድ ልጆቸ አባት ነኝ። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ ማን ይባላሉ ስማቸው?
ዶ//ር እውነት፡እውነት፡- የመጀመሪያው ናትናኤል ጋሻው በዛ ይባላል ። የአራት አመት ልጅ ነው። ሁለተኛው ካሌብ ጋሻው በዛ ይባላል። እሱ ደግሞ የአንድ አመት ተኩል ልጅ ነው። ባለቤቴ ምስጋና ዘኪዮስ ትባላለች፡፡ ትብብርና ለምትጠይቋቸው ነገሮች ፈጥነው የመመለስ ነገራቸው እንዴት ነበር? መልሕቅ፡መልሕቅ፡ ምን ያህል ጊዜ ሆነህ በአሜሪካ? ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ በጣም ጥሩ ጥያቄ ነው። እንደውም በዚህ ላይ ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ ወደዚህ አገር ከመጣሁ ወደ ስምንት ልምዳችንን ለማካፍል የምንፈልገው ከየቤተክርስቲያኖቹ ጋር አመት ሆኖኞል። ከስምንቱ ዓመት አምስቱን ዓመት በትምህርት ፤ ሶስቱን አመት ደግሞ በስራ ነው የቆየሁት የመጨረሻውን ወር ምላሽ (Feedback) ለማግኘት እንሯሯጥ ነበረ።፡ .... በተለይ በኢ-ሜይል መልስ ለማግኘት እንጣጣራለን ። ፡፡ ጥቂት ቤተክርስቲያኖች መልስ ይሰጡናል። ለብዙዎቹ ግን እንደገና ስልክ መደወል ነበረብን። የመጨረሻውን የጠራ ተሳታፊ ቁጥር መልሕቅ፡መልሕቅ፡ የሜዲካል ዶክተር ነህ? እንኳን ለማግኘት ትንሽ ችግር ነበረብን። በዚህ አጋጣሚ ዕድሉን ዶ/ር እውነት፦ የሜዲካል ዶክተር አይደለሁም። ስላገኘሁ እንደ ማሳሰቢያ አርጌ የምሰጠው ተሳታፊ ቤተክርስቲያናት የጂዮ ፊዚክስ ባለሙያ ነኝ:: ከአዲስ አበባ እግዚአብሔር ቢያንስ ሁለት ሳምንት ሲቀረው የመጨረሻውን የተሳታፊዎች በከፈተልኝ ዕድል ሙሉ የነፃ ትምህርት አግኝቼ ወደዚህ ዝርዝር ቢሰጡ ላስታናጋጁ ቤተክርስቲያን በጣም የሚረዳ ነው፡፡ ሀገር በመምጣት ስታንፈርድ ዩኒቨርስቲ ( Stanford መልሕቅ፡university ) ተምሬ የድኅረ ምረቃ ትምህርቴን በ ፒ መልሕቅ፡ ላንተ የትኛዋ ቤተክርስቲያን ነች በብዛት ምላሽ ትሰጣችሁ የነበረችው? ኤች ዲ (PHD) አጠናቅቄያለሁ። መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ጌታ ይባርክህ! ምን ያህል ጊዜ ሆነህ ጌታን ካገኘህ? ዶ/ር እውነት፡እውነት፡- ጌታን ካገኘሁ በጥቅሉ ወደሃያ አመት ይሆናል። መልሕቅ፡መልሕቅ፡ ሒውስተን ቤተክርስቲያን ዘንድሮ ባስደናቂ ዝግጅት ነው የጠበቀችን፤ ምንያህል ጊዜ ወሰደባችሁ ዝግጅቱ? ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ ዝግጅቱን ከጀመርን ወደ አምስት ወር ይሆነናል። ፓስተር ተስፋ በፊት የነበሩ ችግሮችን ወደኋላ ተመልሰን የምናስተካክልበትን ሁኔታና እንዴትም ማስተካከል እንዳለብን ከዚያ ጀምራችሁ በማጥናት ስሩ በማለት አምስት ሰዎችን
መልሕቅ
መልሕቅ፡መልሕቅ፡ የመጨረሻ ጥያቄ ላድርገውና…. እኛ እንደተገልጋይ በጣም ኮርተንባችኋል ባደረጋጃችሁት ዝግጅት እናንተስ ተዘጋጅታችሁ የመጣቸሁበትን ጉዳይ ምን ያህሉን በተሳካ ሁኔታ ፈፅመናል ትላላችሁ? ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ ስንዘጋጅ ብዙ ነገሮችን አብሰልስለናል። ብዙ ነገሮችን ለማስተካከል ሞክረናል። እግዚአብሔርም ረድቶናል በዚህ ሥራ ላይ በጣም የደከሙ ሰዎቸ አሉ። ልባቸውን ፣ ጉልበታቸውን፣ ገንዘባቸውን ፣ አዕምሯቸውን የሰጡ ብዙ ናቸው። በጣም ደስተኞች ነን! ስለሆነው ነገር እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፡፡ ይሄ ስብሰባ ደግሞ የበለጠ ተወዳጅ እንዲሆን እንፈልጋለን። የሚቀጥሉት አስተናጋጆች የበለጠ እንዲያደርጉ ተስፋ እናደርጋለን፡፡
መልሕቅ ፡፡ የመጨረሻው መጨረሻ ጥያቄ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- በዝግጅቱ ወቅት ከተሳታፊ ቤተከርስቲያኖች የምታገኙት ላደርገውና…በዚህች መፅሔት ላይ በዚህ ዝግጅት ውስጥ ሰዎችን ስትመራ ነበርና በግልህ የምታመሰግናቸው ግለሰቦች አሉ?
ለስራ ዝግጁ!
መልሕቅ ፡- ባለትዳር ነህ?
ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ በቤተክርስቲያን ተሳታፊ ቁጥር ብዙ አባላት ያላት የዳላስ ቤ/ክ ብትሆንም የሚገርመው በዘንድሮው ተሳትፎ የሂውስተን ቤ/ክ በልጣታለች። እሱ አሰገራሚ ነገር ነው ። ከሁለት መቶ በላይ የተሳታፊ ቁጥር ከሂውስተን የመጣ ነው፡፡ አዘጋጅም ስለነበረች ብዙም ቅስቀሳዎች ስለተካሄዱም ማለት ነው፡፡
እንኳን ሳይካሄድ ጌታ ኢየሱስ ቢመጣ እኔ እንደው ለኮንፍረንሱ ወጣ ገባ በምልበት ጊዜ ያለኝን ሰዓት እያጠፋሁ ስሮጥ የጌታ ምፅዓት ዝግጅት እንደሚጠይቅ የሚያሳየኝ አንድ መልዕክት አለው። እኔም ለዚያ እዘጋጃለሁ ሰዎችም ይዘጋጁ ። ጥሩ ነገር ነውና በዚህ ሰው ሁሉ እንዲባረክ እፈልጋለሁ፤ ማራናታ ልዩ የሆነ ትርጉም አለው። ብዙዎቻችን በዚህ ሥራ ላይ የተሰማራን ሰዎች የጌታን መገለጥ እያሰብን ፣ የጌታን ሥራን ሰርተን ሲመጣ በደስታ እንሄዳለን የምንል ሰዎች ነን።
ዶ/ር እውነት፡እውነት፡ የኧርቪንግ ( Irving) ቤተክርስቲያን !የተሳታፊዎቹ ቁጥር ጥቂት ቢሆንም ግን የሚያስፈልገውን መልስ በወቅቱ በመስጠት እኔ በዚህ በዘንድሮው ዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢነቴ በጣም እግዚአብሔር ይባርካቸሁ ልላቸው እፈልጋለሁ፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡- ለዚህ ዝግጅት ምን ያህል ገንዘብ አውጥታችኋል? ዶ/ር እውነት፡እውነት፡- በጣም ብዙ ገንዘብ አውጥተናል።፡ ለመስተንግዶውና ለአንዳንድ ነገሮች የወጣውን ትክክለኛ ቁጥር ልነግርህ ይቸግረኛል። አልተዘጋጀሁም ግን ገምት ካልከኝ ከአሰራ ሁለት ሺ ብር በላይ ወጪ የወጣ ይመስለኛል፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡ አንተ በግልህ በዚህ ኮንፍራንስ ላይ ምን በረከት አግኝተሃል? ደ/ር እውነት፡- ማራናታ ለሁላችንም በጣም አስፈላጊ ነው። ዝግጅት ይጠይቃል። እኛም የማራናታን ፕሮግራም ስናዘጋጅ የተባረከውን ተስፋ እያሰብን ነው። ምናልባት ይሄ ኮንፈራንስ
ዶ/ር እውነት ፡- እኔ ማንን ከማን እንደምል አላውቅም።፡ ከፓስተራችን ጀምሮ በዚህ ሥራ ትኩረት በመስጠት በጣም ቀንና ሌት የሰራ ሰው ነው ፓስተር ተስፋ። ሌሎቻችንም በጣም ደክመናል እኔ ዝርዝር ውስጥ ከገባሁ ይከብደኛል። በጣም በጣም ብዙ ሥራ የሰሩ ብዙ ሰዎች አሉ ሁሉኑም ለመዘርዘር ይከብደኛል። ልባቸውን ፣ገንዘባቸውን ፣እውቀታቸውን ፣ ጊዜያቸውን የሰጡ ከሃያ አምስት በላይ የሆኑ ሰዎች አሉ። ሁሉም ለእግዚአበሔር እንደሚሰራ ሆኖ ሰርቷል።፡ጌታ ይባርካችሁ! ልላችው እወዳለሁ የሂውስተን አገልጋዮችን በሙሉ፡፡ .ሥራችንን በተመለከተ መጨረሻ ላይ
ርክክብ ከፓስተር በድሉ ታንቁ ጋር የሁሉን ነገር ማስረጃ ይዘን አንድ ጥራዝ መፅሐፍ አዘጋጅተናል። ዝግጅቱን ዕቅድ ካወጣንበት (brainstorming ) ጀምሮ እዚህ እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ያለውን ነገር በሙሉ ያጠቃለለ ሰነድ ለሚቀጥለው አስተናጋጅ አዘጋጅተናል በዚህም ጌታ ረድቶናል፡፡ መልሕቅ፡መልሕቅ፡ በመፅሔታችን ችን ስም እጅግ አድርገን እናመሰግንሀለን።
ገ ጽ29
ማራናታ!
ክፍተት ሞይው አገልጋይ ማን ልበል ስምህን ? - ጠና ♦ ጠና ማን ? - ጠና ጥሩነህ ♦ ጠና ጥሩነህ ከየትኛው ቸርች ነህ ? - ከካንሳስ ቤተክርስቲያን ነኝ:: ♦ ካንሳስ ውስጥ በምንድነው የምታገለግለው ? - በካንሳስ ውስጥ በወጣቶች አሁን ደግሞ በሽምግልና ♦ የቤተክርስቲይ ሽማግሌ ነህ ? - አዎ ሽማግሌ ነኝ:: ♦ ብዙ ግዜ የምትሠራው ከወጣቶች ጋር ነው ምንድን ነው ወደዚያ ሊስብህ የቻለው ጉዳይ ? -የዛሬ አስራ ሰባት አስራስምንት ዓመት አካባቢ ኮንፍራንሱ ሲጀመር ወጣቶች ብዙም የሚግባባቸው፣ በእድሜያቸው የሚሆን የልባቸውን ሃሳብ የሚረዳ ሰው አልነበራቸውም። እግዚሐብሄር የራሱ ሀሳብ ቢኖረውም በአጠቃላይ እንደ baby sitting በወቅቱ አብሪያቸው ለመሆን ብዬ ነው የተጀመረው። እንደዚህ እያለ ከልጆቹ ጋር አብረን አደግን እንጂ እንዲህ አደርጋለሁ ወይም እንደዚህ ነው በሚል የተጀመረ አይደለም ♦ ዘንደሮ እንዴት ነው ምን ያህል ወጣቶች መጥተዋል ? - ዘንድሮ ከ300 እስከ 350 የሚሆኑ መጥተዋል ። ♦ ወንዶቹና ሴቶቹን በ percentage ብታስቀምጥልን ? - እ እ.. almost እኩል ነው የሚገርመው በሌላ ቦታ ሴቶች ይቀድማሉ ግን እዚህ ሳየው አሁን ግማሽ በግማሽ ይሆናሉ። እኩል ነው! ♦
በምን ዝግጅት ነው የተቀበላችኋቸው? - የዘንድሮውን ዝግጅት ያዘጋጀችው የሒውስተን ቤተክርስቲያን ነች። ቀደም ሲል በኢ-ሜይል የሚመጣውን ሰው ዝርዝር ፣ የፕሮግራሙን ይዘት እንላላክ ነበር። ሒውስተኖች በጣም ተዘጋጅተው ነው የጠበቁን። ጥሩ ነገር ነው የሰሩት። በግሩፕም ፣ በእድሜም ፣ በቁጥርም በተለያየ በመከፋፈል ማለት ነው በደንብ ተዘጋጅተው ነው የጠበቋቸው። ብዙው ነገር እንደ ተዘጋጁበትና እንዳሰቡበት ሄዷል። መልካም ቅበላ ነበር! ♦ ዘንድሮ የኮሌጆቹን ለብቻው ለይታችኋል እርሱ የሚቀጥል ነው ወይስ እንዴት ነው ? -እርሱ እንግዲህ ያው በሚድ ዊስት ቦርድ የሚታይ ነው። እኛ እዚያ ደረጃ ላይ አይደለንም .....I Think የአሁኑ ሙከራ መሰለኝ ። የዳላስ ቤተክርስቲያን ናት ያንን ያደረገችው ዳላስ ያው ቅርበቱም አለ፤ ዕድሜያቸውም ከፍ ከፍ እያለ ሲሄድ ትንሽ ለየት ያለ ትምህርት ያስፈልጋቸዎል ♦
ዓይነቶች ዓይደለም) ለዚያ ነገር የተሰጡ እና ያ ካለመኖሩ
በሚል ነው ሙከራው። መልካም ይዘት ያለው ይመስላል ገና Analyze አልተደረገም ወይም አልተገመገመም። በዚህ ጉዳይ ላይ የሚድ ዌስት ቦርድ የትጋ እንዳለ የሰማነው ነገር የለም።፡ እነርሱ ከገመገሙት በኋላ የሚሆን ነገር ካለ ያው እየቀጠለ ይሄዳል። ለግዜው ግን የዳላስ ቤ/ክ እንደ አጥቢያ ቤ/ክ የራሷን ኮንፍራንስ ነው ያዘጋጀችው ማለት ነው። ♦
አሁን ወደ ግልህ ልምጣና ባለ ትዳር ነህ ? - አዎ
ወንድም ጠና ጥሩነህ ልጆች አላችሁ ? - ልጆች የሉንም ። ♦ ምንድን ነው ከግል ባህሪህ ከልጆች ጋር የበለጠ ደስ የሚልህ ነገር ተፈጥሮህን ንገረኝ እስቲ ዝንባሌህ ? እንግዲህ ልጅ ብቻ አይመስለኝም ነገሩ ፤ ምንድን ነው ሰው መቼም እርዳታ ያስፈልገዋል። በምንም ደረጃ እንደ እድሜው፣ ሕፃንም ያስፈልገዎል ፣ መሐከለኛም ያስፈልገዋል ፣ ሸምገል ያሉትም ያስፈልጋቸዎል። አሁን እንዲያውም ሕብረተሰባችን ወደዚያ እየሄደ ነው። ሽማግሌዎቹም ዕርዳታ መሻታቸው ሊመጣ ነው። እና እርዳታ የሚያስፈልገው ሰው ካለ እግዚአብሔር ካሳሰበን ማድረግ ነው። በወቅቱ ቅድም መጀመርያ ላይ እንደነገርኩህ ሰፋ ያለ need የነበረው ልጆቹጋ ስለነበር ነው ወደዚያ ያዘነበልኩት። አሁን ሳየው እንዳልኩህ በዕድሜያቸውም ደግሞ ገፋ ያሉ ወገኖች ደረጃ እየደረስን ነው...። እነዚያንም ለመርዳት እያየሁ ነው ....ለምሳሌ ሻንጣ ክፍላቸው ማድረስ ከክፍላቸው አውጥቶ አውቶቢስ ማድረስ እነርሱን ማየት መርዳት ብዙ ነገር ገና እየመጣ ያለ አለ ስለዚህ personally የኔ ነገር እንግዲህ የጎደለውን ከማየት አንፃር ነው መሞላት ወዳለበት ነገር መግባት ነው። ♦ አሁን ልጆቹን interview አድርገን ነበር... “አምልኮ አምልኮ ነው የሚደረገው የነበረ ግን አንዳድ fun ያላቸው ነገሮች ቢደረጉ ጥሩ ነው” ይላሉ ምን ትላለህ? እርሱ እንግዲህ የአቅም እና የዝግጅት .... የ full time አገልግሎት ነገር ነው። እኔ እርሱን ነገር ብዙ ግዜ ሳየው ለሚድ ዊስት ኮንፍረስ ለማንኛውም ኮንፍረስ ቀደም ብሎ የስድስት ወር የስምንት ወር ግዜ እቅድና ዝግጅት የሚጠይቅ ነገር ነው። እንደዚያ ያለ Activity በፕላን በደንብ ተሰርቶ ሰዎች ተመድበውለት (ሰዎች ማለት በትርፍ ግዜያቸው የሚሰሩ ትዝ ሲላቸው የሚሰሩ ♦
አንዳንድ መቼም ጉለቶች ወይም እቅዶች የማይከናወኑ አለ ለልጆቹ ብቻ አይደለም ለብዞዎቻችን እንደ ልባችን ምኞትና ሀሳብ የማይሆኑ ነገሮች አሉ። እና እነዛን እንግዲህ ተስፋው ይሄ ነገር እየሰፋ እስከሄደ ድረስ more ደግሞ ሰዎችን እያስገባን በአገልግሎቱ ያንን ያንን የታቀደውን ሰው ካልተቀመጠበት አይከናወንም ስለዚህ እንደዚያ የማድረግ ነው እንጂ ልክ ናቸው በአጭሩ ♦ ባበሻ ወላጆችና ልጆቻቸው መካከል የተፈጠረውን Gap ለመዝጋት ምን ማድረግ ያስፈልጋቸዋል ትላለህ ? ልጆቹን ስንጠይቅ ይወዱናል ግን በጣም ይጨነቃሉ፤ ከመጥፎ ነገር ሁሉ ሊከልሉን ይሻሉ” የሚሉትን ዓይነት ነገር ሰምተናል። አንተስ ምን ትላለህ ? ለወላጆች ምን ቢያደርጉ ነው ጥሩ ብለህ የምታስበው ? - ወላጆች በዚህ ምድር መጥተው System ውስጥ ቶሎ ገብተው፣ ነገሩን ተረድተው፣ ሰርተው፣ Provide የሚደረገውን አድርገው፣ ነገሮችን እንደገና ደግሞ ቀድመው ለልጆቹ ያን ሁሉ ማድረግ መቼም በጣም በጣም የሚያስደንቅ ነገር ነው። በልጅ ዓዕምሮ ባይታይም፣ ልጆቹ ልጆች ናቸውና ሊያዩት ባይጠበቅም ወላጆች ያንን አስቀድመው provide ማድረግ መቻላቸው ትልቅ ትልቅ መስዋዕትነት ነው። አዋቂው established ከሆነ Life ነው የመጣው እንጂ እንደኛ ከ high school አይደለም። ቤቱን ትቶ፣ ሕብረተሰቡን ትቶ፣ ቤተክርስቲያኑን ትቶ ትልቅ sacrifice አድርጎና ኑሮውን አፍርሶ ነው የመጣው። እና እዚህ ደግሞ እንደገና ያንን ለመገንባት minimum አስር ዓመት ይፈጃል ባይ ነኝ። ... I Think አንደኛ የተደረገውን እንደተደረገ ማየት ይረዳል። መቼም ጠላትም ሆነ ሥጋም ሆነ ምንም የሚያስቀድመው የጎደለውን ነገር ነው ግን ወላጆች ብዙ ያደረጉት ነገር አለ። በዚያ መፅናናት አለባቸው። ሌላው Really ሥራው የእግዚአብሔር ነው። .... የሚያድንም የሚናገርም የሚደርስም እግዚአብሔር ብቻ ነው። ስለዚህ ምንድን ነው በርሱ ላይ መታመን ልጆቹም እንደጠቃቀሱት መታመን አለብን። በእግዚአብሔር ላይ ሁላችንም ወጣቶች ነበርን መውጣት መውረድ አለ፤ ግን የ እግዚአብሔር ቃል እስከተዘራ ድረስ ልጆቹን የእግዚአብሔር ቃል ይደርሳቸዋል ብሎ ማመንን ይጠይቃል። ቅዳሜ ለምሳሌ ማለት ነው ትንሽ ቆረስ አድርገው ከሰዓት በኋላ አንድ ልጆችና ወላጆችን የሚያገናኝ ፕሮግራም ቢደረግ ጥሩ ነው። ይሄ ቦታ ትልቅ ነው ፤ ፊት ለፊታችን ነው ያለው እስክ 5000 ሰው ያስተናግዳል፤ ሁላችንም አንድ ላይ ብንሆን ምንም የቦታ ጥበት የለም At least አንድ Program መደረግ አለበት። ...አሁን ያደረጋችሁትን Imagine በ Program ቢደረግ ወላጁ እናንተ የቀዳቹሁትን ቢሰማ Live ማለቴ ነው ያ ነገር ያድሳል፤ ሕብረትን ያድሳል፤ ያጠናክራል ትንሽ ነገር ይመስላል ግን በጣም ብዙ ስራ ነው የሚሰራው በዚያን ሰዓት። ♦ ወንድም ጠና ስለሰጠህን አስተያየት እጅግ አድርገን እናመሰግናለን ። - ጌታ ይባርካቹሁ
ከበታች የተቀመጡትን የልጆች ቃለ ምልልስ እንደአነጋገራቸው ሳንለውጥ ጥሬውን ያስቀመጥንበት ምክንያት ትክክለኛ ገጽታቸውን ላንባቢ ለማሳየት ስንል መሆኑን በትህትና
ገ ጽ30
ፀጉሬን ሉጫ እንዲያደርግልኝ ነው ... ♦
ማነው ስምህ?
◊
ሀብታሙ
♦
ሀብታሙ ማ?
◊
ሀብታሙ ተሰማ
♦
ሀብታሙ ተሰማ የየትኛዋ ቤ/ክ አባል ነህ?
◊
የፓስተር በድሉ!
♦
የዳላስ ማለትህ ነው?
◊
አዎ
♦
መቼ ነው ወደ አሜሪካ የመጣኽው?
◊
አሜሪካ የመጣሁት በ2003 ነው
♦
ኢትዮጵያ ውስጥ የት ነበር የምትኖረው?
◊
ናዝሬት ውስጥ ነበር የምኖረው ግማሽ ሰዓት... ከዛ ደግሞ summer ሲመጣ ወደ አዲስ አበባ ከእናቴ ጋር መቆየት......
♦
እናትህ አዲስ አበባ ናቸው?
◊
እናቴ ናዝሬት ነው ያለችው የእናቴ እናት ነው..
♦
አሃ ! አያትህጋ?
◊
አዎ!
♦
ምን ያህል ግዜ መጥተኻል እዚህ ኦክላሆማ ኮንፍራንስ?
◊
ከ2004 ጀምሮ .. አሁን 2011 ነው ...ወደ አምስት ስድስት ሰባት ግዜ መጥቻለሁ
♦
በመጀመሪያ ደረጃ ምን በረከት አገኘህ?
◊
መጀመሪያ በረከት ያገኘሁት safe መድረሴ ነው። ከዳላስ ተነስተን እዚህ በመድረሴ ደስ ብሎኛል። አሁን ደግሞ በሚቀጥለው ፕሮግራም ከጓደኞቼ ጋር አንድ ላይ በመሆኔ ደስ ብሎኛል።
♦
ዛሬ ነው እንዴ የመጣኽው? /ኦገስት 12/
◊
አዎ ዛሬ ነው። ገና መግባቴ ነው ። ጓደኞቼንም ሁሉንም ገና አላገኘሁም። እስከማገኛቸው እየጠበቅኩ ነው። ከዚያ worship ሲጀመር ወደ worship እንገባለን።
♦
በአምልኮ ለመገልገል ነው የመጣክው ወይስ ጓደኞችህን ለማግኘት ..ለየትኛው ነው ቅድሚያ የምትሰጠው?
◊
ወደዚህ የመጣሁት እግዚአብሄርን ለማምለክና ለመማር ነው የመጣሁት፣ ከዚያ ቀጥሎ ደግሞ ጓደኞቼን አመት ሙሉ ያላየሁዋቸውን እነሱን ለማየት ነው የመጣሁት።
♦ መልሕቅ
ከየት ስቴት ናቸው ጓደኖችህ?
◊
ብዙ ነው ... ከካንሳስ ፣ ምንሶታ፣ ሒውስተን፣ The whole out of place ከዲሲ ከተለያዩ ቦታ የመጡ ጓደኞች አሉኝ።
◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
◊
ሐብታሙ ተሰማ ♦ ◊ ♦ ◊
♦ ◊
♦ ◊
ስለዚህ ስለኮፍያህና ሻሽህ ምን የምትለን ነገር አለ? ኮፍያዬ..... ረጅም ሳቅ ኢትዮጵያዊ ባህል ነው? (ሳቅ ) አይደለም! ፀጉሬን ሉጫ እንዲያደርግልኝ ነው.......እንደ አሜሪካኖቹ አይደለም ያደረግኩት (ሳቅ) አይ ጥሩ ነው! ባለፉት አመታትስ ከዚህ ኮንፍራንስ ምን በረከት አግኝተሃል? ባለፉት አመታት ዎ ....(ዝምታ ) ዎ ... አንድ ነገር ያገኘሁት ጓደኛዬ አብሮኝ መጥቶ ነበር። ጌታን አያውቅም ነበር። ለመጀመሪያ ግዜ ነበር ሲመጣ፣ ከኛ ጋር በመምጣቱ እዚህ ጌታን ተቀብሎ ሄዷል። ከዚያም ዳላስ ስንሄድ አብሮን church ይመጣል። ኢትዮጵያዊ ነው? አዎ ኢትዮጵያዊ ነው። ድሮ ያጨስ ነበር፤ ምን ይል ነበር ፤ አሁን ግን እሱንም አያደርግም።
♦
ምን ያህል ነው ዕድሜህ?
◊
20 አመት ሆኖኛል
♦ ◊ ♦ ◊ ♦
ስንተኛ ክፍል ነህ? Freshman in college ምንድነው የምታጠናው? Criminal justice ወንድም እህቶች አሉህ ?
ሁለት ወንድምና አንድ እህት አለኝ። ማን ይባላሉ? ተስፋሁንና አማኑኤል ይባላሉ። ወደፊት ምን ለመሆን ነው የምታስበው? ወደፊት እንግዲህ ....እኔንጃ! ወደፊት ....በሚመጣው ነው የምሄደው እኔ ፊትህ የመጣውን ነው የምትቀበለው? እግዚአብሄር መንገዴ ላይ ያስቀመጠልኝን ነው የምወስደው ... እዚህ ካሉት ወጣቶች ውስጥ አንዳንዶቹ ጌታን ያላገኙና ለጨዋታ የመጡ ናቸው ትለያችኋላችሁ? I mean አንዳንዱ አለባበሱ ሊለወጥ ይችላል። ለእግዚአብሄር ላይመጣ ይችላል። ግን ከአለባበሱ መለየት አትችልም። የማይሆን ነገር ለብሶ ጌታን የሚያመልክ አለ ፤ በደንብ ለብሶ መጥቶ ጌታን የሚያመልክ የሚመስልና የማያመልከም አለ።
♦
እስከዛሬ የነበረው ምግቡ መኝታው ጥሩ ነው?
◊
እስከዛሬ የነበረው ጥሩ ነው። በጣም! አንድ ላይ ደግሞ የምንጫወተው game ማንም ሳይጎዳ ሁላችንም we had a good time. Everything is good! ስለሰጠኽን ቃለ ምልልስ እናመሰግንሃለን።
ወ/ሮ የሺመቤት አበበ የቤተክርስቲያናችን አባል የወንድም ዮሴፍ ራፋት ወላጅ እናት ሴፕቴምበር 6 ቀን 2011 ዓ/ም ወደ ጌታ ሄደዋል። አስከሬናቸው ወደ ሀገር ቤት ተልኮ የቀብር ስርዓታቸው ተፈጽሟል። ለመላው ቤተሰባቸው መጽናናት ይሁን! እኚህ ሰው የ7 ልጆች እናት፣ የ19 ልጆች አያት፣ የ6 ልጆች ቅድመ አያት ነበሩ።
ገ ጽ31
ማራናታ!
ከአባቷ በላይ ትምህርት የምትወደው ሕፃን ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
ርብቃ እንዳለ ሻቃ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
ማን ልበል ስምሽን? ርብቃ! ርብቃ ማ? ርብቃ ሻቃ! ስንት ወንድምና እህቶች አሉሽ? አንድ እናት... አንድ አባት ሁለት እ እ እ / ያልጠየቅናትን መልሳ አሳቀችን/ ስንት ወንድም አለሽ? ሁለት እህትስ? እህት የለኝም የት ነው የተወለድሽው? የመን ስንት አመትሽ ነው? ሰባት እንዴት ነው እንደዚህ አማርኛ ጎበዝ የሆንሽው?
◊ ♦ ◊
♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
እናቴ ታስተምረኛለች አባትሽስ? እሱም ያስተምረኛል ሌላ ምን ቋንቋ ትሽያለሽ? የመን ነው የተወለድሽው አረብኛ ትናገሪያለሽ? ኖ እንግሊዝኛ ትችያለሽ? እህ ስንት ግዜ መጥተሻል እዚህ ኦክላሆማ ሁለት ግዜ ምን ትምህርት ተማርሽ? ለሰው ምግብና Cloth ካመጣን poor people (ለድሆች) እንሰጣለን። ደሀዎችን መርዳት ነው ያስተማሯችሁ? እህ ሌላስ? እሱን ብቻ ነው። ጓደኛ አገኘሽ እዚህ? አዎ ከሌላ ከተማ የመጣች? I don’t know ሌላ ምንድነው ያስደሰተሽ ነገር? ዝም
◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
ደስ ብሎሻል እዚህ ስለመጣሽ?
♦
የመጀመሪያ ተሳትፎን በአገልግሎት... ኢዮብ ነጋሽ ♦ ማን ልበል ስምህን ? - ኢዮብ ነጋሽ ♦ ከየትኛው ቤ/ክ ነህ? - ሒውስተን ♦ ምን ያህል ግዜ ተለማምዳችኋል ይሄን መኪና ለማሽከርከር? - ይሄን መኪና ለማሽከርከር እኛ ቤ/ ክ ውስጥ ride አገልግሎት ይሰጣል። በዚያ ውስጥ እኔና አንድ ወንድም አብረን እንሰራለን። ከግቢው ውጭ ፓርክ ስለምናደርግ ከመኪና ማቆሚያው እስከ ቤ/ ክ / shuttle service/ ለመስጠት ይሄን መኪና ብዙ እንነዳ ነበር። ♦ ባለትዳር ነህ? - አዎ ♦ ስንት ልጆች አሉህ? - ሶስት ♦ ማነው ስማቸው? - ቤርሳቤት ፣ ኤፍራታና ዳግማዊ ♦ ባለቤትህስ ስሟ ማነው? - ብዙ ወርቅ
በምታመላልሱበት ግዜ ሕዝቡ ስለኮንፍራንሱ ምንድነው የሚያወራው? - ሕዝቡ በጣም ደስተኛ ነው። ከአርብ ዕለት ጀምሮ እግዚአብሄር ከኛ ጋራ እንደነበረ ብዙ ይጨዋወታሉ ። ♦ ሕዝቡ እርስበርስ ያወራል.. - አዎ! በጣም! ♦ በቀን ውስጥ ምን ያህል ግዜ ከአዳራሽ ወደ ምግብ ቤት ትመላለሳለህ ? - ቀኑን ሙሉ? ከ400- 500 ግዜ ♦ 400 ግዜ ይሆናል? - አዎ! ♦ (ሳቅ) ግምታችሁ በጣም ይለያያል አንዱ 25 አለኝ አንተ 400 ፣ ሀያ አምስትም በጣም ያንሳል አራት መቶም ይበዛል.... ♦ በነገራችን ላይ ስንተኛ ኮንፍራንስህ ነው? - እኔ ስመጣ የመጀመሪያዬ ነው ♦
◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊
እህ ምኑ ነው ደስ ያለሽ? እንትን እ እ እ food
ምግቡ አሪፍ ነው? እህ መኝታውስ ተመችሽ? እንቅልፍ በደንብ ወሰደሽ? እህ በሚቀጥለው ዓመት መምጣት ትፈልጊያለሽ? አዎ! አንቺን ደስ ያለሽ ነገር ምንድነው? ጨዋታ አልተጫወታችሁም? ጨዋታ ነገር አዎ ምን ተጫወታችሁ? Game አሸነፍሽ? አዎ! ስንተኛ ክፍል ነሽ? ሁለት ትምህርት ትወጃለሽ? አዎ ከዳዲና ከትምህርት ማንን ነው የምትወጂው? ትምህርት! / ይሄን አያቅም ነበር መሰለኝ አባቷም ተገርሞ ሳቀ/ ርብቃ እጅግ አድርገን እናመሰግንሻለን!
♦ ምንድነው ያገኘኽው በረከት? - በአሜሪካን አገር እንደዚህ ክርስቲያኖች ተሰብስበው ሳይ ለመጀመሪያ ግዜ ነው። እናም እኔ ለራሴ በጣም ተባርኬበታለሁ። ♦ ስለሰጠኽን ማብራሪያና ስለአገልግሎትህ እናመሰግንሃለን!
ኢዮብ ነጋሽ የመጀመሪያ ተስታፊ
ገ ጽ32
የሁለት ከተሞች ጓደኛሞች መልሕቅ - ማነው ስምሽ? ሃናሃና ይሄ ሶስተኛዬ ነው መልሕቅ ምንድነው ያገኘሽው በረከት በኮንፍረንሱ? ኪያኪያ እኔ አሁን የእኔ ሕይወት ላይ እግዚአብሔር ብዙ ነገር ስለሆነብኝ like ሕይወት በጣም school ምናምን ስለማደርግ ለእግዚአብሔር time የምሰጠው ጠፋብኝ።ለእግዚአብሔር
ኪያ ቶሎሳ
አልሰጠውም። እዚህ ስመጣ ነገርኩት። ከመጣሁት በፊት እኔ
ኪያ - ኪያ ቶሎሳ
ማግኘት የምፈልገው አንተን ነው፤
መልሕቅ- አንቺስ
አንተን ማውቅ ነው የምፈልገው ፤
ሃና - ሃና ሰሎሞን
አንተ እኔን ከልቤ ታውቀኛለህ። አንተ
መልሕቅ - ጓደኛሞች ናችሁ?
እንደምታውቀኝ እኔ ደግሞ አንተን
ሃናሃና- እኔ እዚህ ሚድ ዌስት ደስ የሚለኝ like ሁል ጊዜ ዓመቱን ሁሉ on off ብሆንም እዚህ ስመጣ ሁልግዜ እታደሳላሁ። ሁሉም ከ different state ሲመጡ ይፀልዩልሃል ፣ ያዋሩሃል you know like እግዚአብሔር በእነሱ በኩል አልፎ ይናገርሃል።፡ its like በጣም ጥሩ ነው፤ ምክንያቱም ድጋሚ እነሱ ሁሉም ሰው አንድ ዓይነት ብቻ አይደለም you know ሂውስተን ሁሌ አንድ ዓይነት ነን :: ግን እዚህ experience ምናምን ይነግሩንና ከዛ እግዚአብሔር እንደዚህ እንደዚህ ብሎ ይናገርሃል so Midwest ለእኔ መታደስ ነው።
እፈልጋለሁ ነው ያልኩት ። እናም like እዚህ ስመጣ እዚህ pray እያረግን
መልሕቅመልሕቅ- ሃናስ ?
ኪያኪያ እኔ እዚህ ስመጣ ከነሱ ጋር መተኛት ይሄኛው የfirst year ነው የእኔ እናት አባቶች Hotel rent እናደርግና እዛ ነው የምንቀመጠው እዚህ ከነሱ ጋር አልነበርኩም። ስለዚህ አሁን ከነሱ ጋር stay ስለማደርግ ሴቶቹን ማወቅና በየት እንደሆኑ አውቄያለሁ
ነበር እና በቃ ፓስተር እግዚአብሔርን
መልሕቅ - እሷን ዛሬ እንዴት ጓደኛ ልያታደርጊያት የቻልሽው ነው
በኋላ last night pray ስናደርግ ነበረ።
ኪያ - ኦ ሳቅ she’s very sweet እሷ she’s all smiling …..በጣም
እግዚአብሔር እንዴት feel
ሃናሃና- ህእኔ አሁን ያልወደድኩት ነገር High school college people አንድ ዓይነት አልሆኑም ማለት ነው እኔ አሁን ወደ college ነው የምሄደው ለዛ የመጨረሻዬ ነው ግን mid west በጣም ደስ ይላስ ምክንያቱም ሕፃናቶች ራሳቸው ለእግዚአብሔር ያላቸውን እያየህ ደስ ይልሃል። እሷ ያለችውን ነገር በጣም agree አደርጋለሁ because activity ሲኖር ብዙ ስናደርግ activityያችን በመጽሐፍ ቅዱስ ምናምን you know እንደሱ ዓይነት activity ብናደርግ በጣም ጥሩ ይመስለኛል
መልሕቅ - አንቺ ከየት City ነሽ? ኪያኪያ- ከዳላስ መልሕቅ - አንቺስ? ሃና - ከሒውስተን መልሕቅ - በየዓመቱ ነው የምትገናኙት ወይስ ዘንድሮ ነው የተገናኛችሁት? ኪያ - ዘንድሮ ነው የተገናኘነው አላየሁሽም
ኮንፍራንሱ ያስተዋወቃቸው ጓደኛሞች
ሃና - እኔ ግን አይቻለሁ last year እሷ አላየችኝም መልሕቅ - ምንድነው ጓደኛ ልትሆኑበት የቻላችሁበት ምክንያት
መልሕቅመልሕቅ እሱ ነው የሳበሽ ?
ማወቅ
feel የሚያደርገውን ነገር እናንተም feel ካረጋችሁ ሌላ ሌላ ቦታ ይወስዳችኋል እያለን ነበረ። ከዚያ
አንድ ልጅ አንድ ነገር ሲል በቃ በጣም
እንደሚያደርግ አሳወቀኝ። በኔም
ኪያ አዎ!
ሕይወት ፣ በጓደኞቼም ፣ እንዴት feel
ሃናሃና እሷ ደስ ያለችኝ like ስንፀልይ ምናምን ለእግዚአብሔር ያላት ነገር በጣም ጥሩ ነው። እና ስንፀልይ Hand shake ምናምን ስንሰራ I just ጥሩ ልጅ መሆንዋን አውቅሁኝ ከዛ I was like OK!
እንደሚያረግ አወኩትና አስለቀሰኝ
መልሕቅመልሕቅ- ምን ያክል ጊዜ እዚህ ኮንፍረንስ መጥታችኋል?
መልሕቅ
። እግዚአብሔር እንዲያወራኝ እሱ feel እንደሚያደረግ እንዳውቅ ነበር የፈለግሁት መልሕቅመልሕቅ-
አንቺስ?
ሃና - እኔ የተማርኩት አርብ ዕለት ይሁን ቅዳሜ በጣም ደስ ያለኝ መልክት ማለት ነው you know ያች ሴት ደም የሚፈሳት የነበረችው ኢየሱስ ክርስቶስን ነካችው አይደል? ያንጊዜ እየሱስ ክርስቶስ “ማን ነው የነካኝ?” አለ። “እንዴት እንደዛ የነካኝ ትላለህ ሁሉም
መልሕቅ - በጣም የሚገርም ነው።፡ እንዴት ? ኪያ የእኔ አስተያየቴ ይሄ program በጣም ጥሩ ነው ። ልጆች ኢየሱስን ያውቁታል እና በጣም ብዙ ነገር። አሁን ገና ነው activity የጀመርነው እና አንድ ቦታ የምንሄደው like አሁን እኛ ኢየሱስን አውቀነዋል ፤ ስለዚህ ከሱ ጋር worship ማድረግ it’s ok for us ግን የሚመጡት ሰዋች camp ሲሄዱ O camp ነገር እናደርጋልን camp ነገር እናደርጋለን worship ብቻ አይደለም የሚሆነው ብለው መጥተው worship ብቻ ሲሆን thay don’t really likes that …they will say O am not going to come back next year it’s ok but I am not come back next year እና ስለዚህ ከቻላችሁ more fun ካረጋችሁትና more activity ካረጉልን like ልጆቹ ይሳባሉ ። እዚህ ይመጡና ለfun የሚመስላቸውን ነገር እግዚአብሔር really ይቀይራቸዋል
ኪያ አዎ እዚህ ነው የተዋወቅነው
መልሕቅ - በዘንድሮ ኮንፍረንስ ጭንቅላትሽ ውስጥ የቀረ የተለየ ነገር ምንድነው?
መልሕቅ - አለዚያ boring ይሆንባቸዋል ለሌሎቹ ነው የምትይን? ሃና—Yeah not just boring ግን ሃና worship worship worship ከሆነ ልጆች ሰለሆኑ ይሰለቻቸዋል እኔ 18 ዓመቴ ነው I understand but ግን እንደዛ ቢሆን ጥሩነው በጣም ለልጆቹ ማለት ነው ለዛ ነው።
ሐና ሰለሞን
እየነካህ ነው” አሉት ሰዎቹ ። እሷ የነካችው ማለት ነው ከልቧ ነው እሱ feel አደረገው so እኛ ሁል ጊዜ ንካን ንካን ማለት ሳይሆን እኛ ራሳችን ኢየሱስን መንካት አለብን you know በምናደርገው ነገር ከልብ that is what የተማርኩት እና ድጋሚ activity ትንሽ አድርገናል that is good ደስ ብሎኛል መልሕቅ - ኪያስ? Yesterday teach ያደረገው pastor መልሕቅ ማነው ስሙ? ኪያ—ፍልፕስ ኪያ እዚአብሔርን feel አላደረግሁትም እያልኩ ነበር ከእኔ ሕይወት ላይ እና ያስተማረው ነገር የእግዚአብሔር ደግሞ እንትን በtime በseason እዚአብሔር እዛ ጋር ነው fallም ሲሆን winterም ሲሆን whenever like dry season ሲሆንብሽ አንቺ እዚአብሔርን feel አላደርግም እዚህ ጋር አይደለም አይናገረኝም ስትይው አንቺ press ማድረግ አለብሽ አንቺ more መሄድ አለብሽ እና ውሃ ከሌለው አትክልት ground ውስጥ ውሃ ፍለጋ more ይሄዳል እንጂ quit አድርጎ አይሞትም ። እና ደግሞ እኔን እንደዚያ ነው ያስተማረኝ። እግዚአብሔር like አንቺ feel አታደርጊውም አይናገርሽም እንደዛ feel ካረግሽው የ dry season ሽ ነውና like ውስጥ መግባት አለብሽ። እግዚአብሔርን ፈልገሽ ውስጥ መግባት አለብሽ መልሕቅ - Thank you so much ስለ ሰጣችሁን ቃለ ምልልስ እግዚአብሔር ይስጥልኝ! ሁለቱምሁለቱም- Thank you
ገ ጽ33
ማራናታ!
የነገዋ ሚሽነሪ ♦ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊
♦ ◊
♦ ◊ ♦ ◊
♦ ◊ ♦ ◊
በጣም በጥሩ ሁኔታ ስለሆነ መጥፎ ነገር ማለት አልችልም። መጥፎ ነገር ሳይሆን የሚስተካከል ነገር ነው የጠየቅንሽ
ቅን አገልጋይ ! ♦
ማን ልበል ስምህን
ቤቴል
◊
የሺጥላ ኋይሉ እባላለሁ
ቤቴል ማን?
♦
ስንተኛ መንጃፍቃድ ነው ያለህ?
መሐመድ
◊
እዚህ አገር መንጃ ፍቅድ ቁጥር የለውም
♦
በቀን ውስጥ ምን ያህል ጊዜ ከምግብ ቤት ወደ አዳራሹ የተመላለስክ ይመስልሃል?
◊
አልቆጠርኩትም
አሁን በጌታ ነው ያለው?
♦
በግምት?
አዎን!
◊
በግምት ከሃያ እስከ ሃያ አምስት ጌዜ
♦
ምንድነው የሕዝቡ አስተያየት ስለኮንፍረሱ ፣ ይዘሃችው ስትሄድ ምንድነው የምትሰማው?
◊
የሺጥላ ጥሩ ስርቪስ እንደሰጠን ነው የሚያወሩት ። ዌዘሩም ጥሩ እንደሆነላችው በሁሉ ነገር
ማነው ስምሽ?
ከሙስሊም ቤተሰብ ነሽ? አይደለሁም አባትሽ እንዴት መሐመድ ተባለ? ድሮ ሙስሊም ነበር።
እናትሽስ? እሷም በጌታ ነች ሙስሊም ነበረች እሷም?
ቤቴል መሐመድ
አይ አልነበረችም እሷ ጌታን አግኝተሻል? አዎ አግኝቻለሁ ጌታን መቼ ነው ያገኘሽው? ኦ... እኔ አስር ዓመቴ ሲሆን አሁን ዕድሜሽ ስንት ነው? 18 የስንተኛ ክፍል ተማሪ ነሽ?
◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
አሁን ኮሌጅ ውስጥ ነኝ። ስንተኛ ዓመትሽ ነሽ?
◊
የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ነኝ።
♦ ምንድነው እስከዛሬ ድረስ ከዚህ ኮንፍራንስ ያገኘሽው በረከት? መዓት ነው ያገኘሁት! እ እ እ ከዚህ በኋላ ሳድግ ◊ ምን እንደማደርግ፣ በስራ ቢሆንም ፣ ስለቤተሰቤም ብዙ ፣ ስለጓደኞቼም ብዙ ♦ ተምሪያለሁ ምንድነው ከኦክላሆማ ኮንፍራንንስ ከልብሽ ◊ የቀረው ትምህርት? ♦ የተማርነውን ነገር ለራስህ ለመውሰድ ብቻ ◊ ሳይሆን ለሌላም ሰው መንገር እንዳለብህ የሚለው ♦ ነው ◊ ከየትኛው ከተማ ነው የመጣሽው? ከዳላስ ወላጆችን በተመለከተ ልጆቻችንን በማሳደግ ሂደት ውስጥ የምትመክሪን ነገር አለ? ♦ ልጆቻችሁ አንዳንድ ነገር ሲነግሯችሁ ስሙ! (ሳቅ) መዓት የሚሉት ነገር ዝም ብለው አይደለም ◊ ሲቀልዱም አይደለም፤ በቀልድ ብቻ አይደለም የሚያወሩት፤ አንዳንድ ግዜ የዕውነት ነገር ነውና የሚሉት በደንብ ሰምታችሁ አንዳንድ ነገር እንድታግዟቸው ነው የምመክራችሁ! ልጆች የሚሉትን ወላጆች እንዲያዳምጡ እያልሽን ነው? አዎና ! ኢትዮጵያውያን ወላጆች ልጆቻቸውን በማሳደግ ውስጥ ያሉበትን ሁኔታ እንዴት ትገመግሚዋለሽ? እኔ መጥፎ ነው ብዬ አላስብም። ጥሩ ነው ብዬ ነው የማስበው። የኔ እናትና አባት ያሳደጉኝ
እንደተባረኩ ነው የሚናገሩት ሰዎቹ
የሚስተካከልም ብዙም የለም። እዚህ ኮንፍራንስ ስንት ግዜ መጥተሻል ?
♦
ምን ያህል የጎልፍ መኪናዎች ነው የምታሽከረክሩት
◊
የተሰጡን መኪናዋች ወደ አስር ናችው
12 ዓመት ሲሆነኝ ነው መምጣት የጀመርኩት። ትምህርት ቤት እንዴት ነው ውጤትሽ? ጥሩ ነው ስለዚህ ኮንፍራንስ ስታስቢ ምኑ ነው ይበልጥ የሚናፍቅሽ? ድሮ የነበረው ለራሴ ነው አሁን ደግሞ ለሌላ ልጆች የሚያስፈልገውን ማገዝን ነው ቤተ ክርስቲያንሽ ውስጥ ምንድነው የምታገለግይው? በቅርብ ግዜ ወደ ኢትዮጵያ ሄደን ነበር። አብረን እንደ mission trip እና አዚያ ስንሄድ like orphanage ልጆች ጋር ሰርተን ነበር.. ኢትዮጵያ ውስጥ የት አካባቢ?
የሺጥላ ኃይሉ ባገልግሎት ላይ
አዲስ አበባ ምን ይባላሉ ድርጅቶቹ? መዓት ናቸው እስቲ የምታስታውሽውን ንገሪን? ከቤዛ church ጋር ሰርተን ነበር። ሌላ peter’s home የሚባል ቦታ ሄደን ነበር። YFC / youth for Christ / የሚባሉ ቦታ ሄደን ነበር። ከሌሎችም ሚኒስትሪዎች ጋር ሰርተን ነበር። በቃ ወደ አገልግሎት ውስጥ ሰምጠሻል ማለት ነው አዎ! ጌታ ይባርክሽ! ልጆቻችሁ አንዳንድ ነገር ሲነግሯችሁ ስሙ! ... መዓት የሚሉት ነገር ዝም ብለው አይደለም ሲቀልዱም አይደለም፤ በቀልድ ብቻ አይደለም የሚያወሩት፤ አንዳንድ ግዜ የዕውነት ነገር ነውና የሚሉት በደንብ ሰምታችሁ አንዳንድ ነገር እንድታግዟ እንድታግዟቸው ነው የምመክራችሁ! ቤቴል መሐመድ
♦
ምን ያህል ጊዜ ዝግጅት አድርጋችኋል?
◊
በአንድ ወር ውስጥ አካባቢ ውስጥ በተራ በተራ ሂውስተን ውስጥ ጎልፍ ካርት ስላለን ልምምድ እናደርግ ነበረ።
♦
ጎልፍ ካርት እዛው ነው ተለማምዳችሁ የመጣችሁት?
◊
አዎ ብዙዎቻችን እዛው ተለማምደናል
♦
ስለ ኮንፍረንስሱ ምን ትለናለህ?
◊
እኔ የመጀሪያዬ ጊዜዬ ነው። በጣም ጥሩ ሆኖ ነው ያገኘሁት። በጣም ነው ደስ ያለኝ የበረከት ዓመት እንደሚሆንልን ለሁላችንም ተስፋ አደርጋለሁ
♦
ካገለገላችሁ በኋላ ገብታችሁ ትካፈላላችሁ ኮንፍረንሱን
◊
አዎ! ሰርቪሳችንን ስንጨርስ ሁላችንም ገብተን እንካፈላለን
♦
ውንድም የሺጥላ ስለሰጠኽን አስትያየትና አገልግሎት እናመሰግናለን!
ገ ጽ34 ገ ጽ34
የመጣነው እግዚአብሔርን ለማግኘት ነው!
ማን ልበል ስምሽን? እመቤት ጣሰው ከየትኛው ቤ/ክ ነሽ? ከብርሃነ ወንጌል ቤ/ክ ቺካጎ ስንት ግዜ ተካፍለሻል በዚህ ኮንፍራንስ? በዚህ ኮንፍራንስ ስካፈል የመጀመሪያ ግዜ ነው ድሮ የቺካጎን ኮንፍራንስ ትካፈይ ♦ ነበር? አልደረስኩበትም እንዴት አገኘሽው ኮንፍራንሱን? በጣም ልዩ ነው! ...ማለት ለመምጣት ብዙም ፍላጎት አልነበረኝም ግን በእግዚአብሄር ፈቃድና ፕላን እዚህ ቦታ ተገኝቻለሁ። ከጠበቅኩትና ከገመትኩት በላይ ነው እግዚአብሄር የሰራው ፤ እግዚአብሄር ደግሞ በድንቅ ሁኔታ በተለየ መልኩ ሊያስተምረን እዚህ ስፍራ ላይ እንዳመጣን ተረድቻለሁኝ። በዕውነት ድንቅ ግዜ ነው! ለራሴ ቃል ገብቻለሁ ከቤተሰቤ ጋር በሚቀጥለው ኮንፍራንስ ለመምጣት። በጣም ደስ ይላል! እስከዛሬ ድረስ ከተማርሽው ልብሽ ውስጥ የቀረ ◊ ላገኘሽው ሰው ሁሉ የምትነግሪው የትኛው ትምህርት ነው? ዋናው ነገር ትላንትም ከትላንት ወዲያም ዛሬም ስንማር የነበረው ስለ ጌታ ምጽዓት ነው። እና ግዜው ነውና ሰዓቱ ነውና እግዚአብሄር በሰዓቱ ያለውን ነገር ለኛ እየሰጠን
♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊
♦
◊
ስለሆነ የቀረ ነገር የተረሳ ሰዎችም ደግሞ ከፍርሃትም ይሁን ከምንም የተነሳ ይሆን አላውቅም ወደኋላ ያስቀረነውን ነገር እግዚአብሄር እያነቃቃን እንዳለ ..በዚህ ጉዳይ ላይ እግዚአብሄር በብርታት የተናገረን ነገር እንደሆነ ነው የቀረልኝ ቃል። ሁለተኛው ደግሞ የሞተው የተረሳውን ነገራችንን እንድንነቃ እግዚአብሄር የማነቃቂያ ግዜ እንዲሆነን ያዘጋጀልን መሆኑ ነው። የመጀመሪያ ግዜዬ ነው ብለሽኛልና ♦ ◊ ♦ ◊
እመቤት ጣሰው ምግቡ መኝታው እንዴት ነበር? እግዚአብሄር ይመስገን በጣም ልዩ ነው! መኝታው ማለት ..... ከምንጠብቀው በላይ ሆኖልናል። ባይሆንም እንኳን የመጣንለት ዓላማችን እግዚአብሄርን ለማግኘት፣ የእዚአብሄርን ቃል ለማግኘት ነው እንጂ የመጣነው ለመብላት ለመጠጣት አይደለም ። በዚህ ስፍራ ላይ
♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦
እግዚአብሄር ለየት ባለ መልኩ ክምንባክንበት ማለት አሁን አገራችን ብዙ ኮንፍራንሶች አሉ ፣ ብዙ ፕሮግራሞች አሉ ..ከኮንፍራንስ በኋል ስራ ለመግባት እንሞክራለን ቤተ ልጆቼ እንላለን።ብዙ ነገር አለ። እዚህ ስፍራ ላይ ግን በተለየ መልኩ ግዜያችንንም ፣ ሰዓታችንንም ፣ ላባችንንም፣ መንፈሳችንንም እዚህ ቦታ ላይ አድርገን እግዚአብሄርን እንድናመልክ የተሰጠኝ ግዜ መሆኑን እረዳለሁ። ይሄንን አገልግሎት ለማግኘት ምን ያህል ሰዓት ነድታችሁ ነው የመጣችሁት? ወደ 18 ሰዓት 18 ሰዓት ነድታችሁ ያገናችሁት በረከት ይመጥናል? ይበልጣል! ለኔ በልጦብኛል። ምንም አልተሰማኛም። ባለትዳር ነሽ? አዎ ስንት ልጆች አሉሽ? የአንድ ሴት ልጅ እናት ነኝ። ስንት ዓመቷ ነው ልጄ 21 ዓመቷ ነው። ከ Loyola university ተመርቃለች። ጌታ ይባረክ! አሁን ደግሞ medical school ትሄዳለች። ፓስተርሽ ማነው? ፓስተሬ ፓስተር ገነቱ ይባላል። ፓስተር ገነቱ ደግሞ ለኛ እንደ ሁለተኛ ፓስተራችን ነው! ብዙ አገልግሎት ሰጥቶናል። ስለሰጠሽኝ ቃለ ምልልስ ጌታ ይባርክሽ! ጌታ ይባርካችሁ! ተባርከናል! እግዚአብሄር ፀጋውን ያብዛልን! አሜን!
“የተማርኩት የተማርኩት መንገዴን እንድቀይር አሳመነኝ አሳመነኝ”... ”... - ማን ይባላል ስምህ? - እስጥፋኖስ እባላለሁ - እሲጥፋኖስ ማን? - አድነው
- ጭንቅላትህ ውስጥ የቀረ ነገር ካለ እስቲ ሰዎቹ ከሚያዋሩት ትንሽ ንገረኝ? - በርግጥ እንደዚህ ነው እስካሁን ያልኩት ነገር የለም ራሴም ተጫዋች ስለሆንኩ ብዙ..
ጓደኛ ማግኝት የምንችለው” በሚል ርዕስ ላይ ብዙ ነገር እንትን ብሎናል እና ወጣቱን በጫንኩ ቁጥር ሁሉም ውይይቱ በዛ ላይ ነው - አንተ ባለትዳር ነህ?
- ምን ያህል ጊዜህ ነው አሜሪካ ከመጣህ?
- አይደለሁም
- አምስት ዓመቴ ሆኖኛል
- ሚስት ነዋ የምትፈልገው በዛው? ሳቅ
- እዚህ ኮንፍረስ ስትካፈልስ?
- እያፈላለኩ ነው! ሳቅ
- ይሄ አራተኛዬ ነው
- እንዴት ነው ሁኔታው?
ምን ያህል ጊዜ ትመላለሳለህ ካዳራሹ ወደ
- በትምህርቱ ብዙ ዕውቅት ቀስመናል! ምክንያቱም ከዚህ በፊት እጠቀምበት የነበረውን መንገድ ሁኔታ ትላንትና በተማርኩት መንገድ ትልቅ ትልቅ ለውጥ አለው ብዬ አምናለሁ
ምግቤት? - ከአርባ - ሃምሳ ጊዜ እመላለሳልሁ - በምታመላልሳቸው ጊዜ ምንድነው ሕዝቡ የሚያወራው ? ስለኮንፍረንሱ... - ያው ብዙን ጊዜ የራሱን ጨዋታ ነው የሚጫወተው - ስለ ኮንፍረንሱ ሲያወሩ አትሰማም እርስ በርስ? - እሰማለሁ ያው ስለ አግልግሎቱ፣ ስለ አስመላኪዎቹ ፣ስለነበረው ፕሮግራም
መልሕቅ
እስጢፋኖስ አድነው - በአንተ ዙሪያ ነው የምታስወራቸው? - አዎ! በእኔ አርእስት ነው የማዞራችው ... by the way like ወጣቶችን በጫንኩበት ሰዓት ትልቅ ነገር ትላንትና ፓስተር እንድርያስ ስለ ወጣቶች “እንዴት ነው የትዳርን
- ሌላስ በግልህ ባግልግሎት የተባረክበት ፣ የመሰጠህ ከዚህ ኮንፍራንስ ውስጥ? - ሰው ከአምልኮ ላይ ሆኖ ምንድነው የሚባለው ወደ ቅዱሰ ቅዱሳን ሲገባ... ያን ነገር በጣም ያስደስተኛል! ያንን ነገር መማሬ በጣም ደስ ብሎኛል
- እጅግ አድርገን እናመሰግንሀለን!
ገ ጽ35
ማራናታ!
ብሩህ ቀና ወጣት ! ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊
♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊ ♦ ◊
♦
◊ ♦ ◊ ♦
◊
♦
ማነው ስምህ? ናትናኤል ኢሳያስ ናትናኤል ኢሳያስ ከየትኛው ቤ/ክ ነህ? ከሒውስተን ማነው ፓስተርህ? ፓስተር ተስፋ እዚህ ኮንፍራንስ ምን ያህል ግዜ መጥተሃል? አንድ 6 ዓመት የት ነው የተወለድከው? ኢትዮጵያ ነው የተወለድኩት ግን ፍሎሪዳ ነው ያደግኩት ወደ አሜሪካ ስትመጣ ስንት ዓመትህ ነበር? ስድስት.... ሰባት አማርኛ ግን በደንንብ ትናገራለህ....እንዴት ሊሆን ቻለ? አዎ አ አ like every summer እዚያ እንሄድና ብዙ እዚያ ስለምንቆይ እንትን አልልም አልረሳም። እቤትም በአማርኛ ነው የምናወራው ኢትዮጵያ ነው የምትለኝ? አዎ! ለ Summer vacation ምናምን ስንተኛ ክፍል ነህ? እኔ አሁን ኮሌጅ ገባሁኝ ጌታን አግኝተሃል? አዎ አግኝቼያለሁ መቼ ነው ያገኝኽው? ከሁለት አመት በፊት ምንድነው አሁን የተባረክበት ጉዳይ? እዚህ በመምጣቴ በጣም ብዙ ወንድምና እህቶች አግኝቻለሁ። በሕይወቴ ውስጥ ያለፍኩባቸው አንዳንድ ነገሮች እኔ ብቻ እንዳልሆንኩኝ እነሱም ልክ እንደኔ የተሰማቸው መሆኑን አይቻለሁ የሕይወቴን ገጠመኝ በሌሎችም ሕይወት ውስጥ አይቼ ብቸኛ እንዳልሆንኩ ገባኝ ነው የምትለን? አዎ ስለዚህ ኮንፍራንስ ስታስብ የምትናፍቀው ነገር ምንድነው? ሁላችንም አንድላይ ፊት ሆነን worship ስናደርግ ደስ ይለኛል። እዚህ ኮንፍራንስ ላይ ሁሉም የሚመጡት ጌታን ያገኙ አይደሉም .. ለጨዋታ የሚመጡም አሉ ትለያችኋላችሁ? አንለያቸውም! እነሱንም ልክ እኛ ከመጀመሪያ እዚህ ከመጣን በኋላ እግዚአብሄርን እንዳገኘን እነሱም the same way እንዲያገኙ እንረዳቸዋለን። ጌታን ያገኘኽው ኢዚህ ኦክላሆማ ኮንፍራንስ ላይ ነው?
◊
♦
◊
♦
◊
♦ ◊
አይደለም። ቤተሰቤ ክርስቲያን ናቸው። በክርስቲያን ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደግኩት። ለረጅም ግዜ እኔም ክርስቲያን ነኝ ብዬ ነበር እንትን የምለው... ከሁሉም ጋር እንደ ክርስቲያን ነው act የማደርገው ግን ውጭ ለብቻዬ ስሆንና ከክርስቲያኖች ጋር ስሆን አንድ አልነበርኩም ። ባህርዬ ይለዋወጥ ነበር። አሁን ግን ያው አንድ አምላክ ነው የምናመልከው ....በጌታ መሆኔን ለነሱም አሳውቃቸዋለሁ። መጥፎ ነገር ምናምን እናድርግ ቢሉኝ “ አይ እኔ እንደዚህ ዓይነት ነገር አላደርግም ...ከእግዚአብሄር ጋር ነው ያለሁት እላቸዋለሁ። እነሱንም ደግሞ እንዳያደርጉ ፣ ከክፉ ነገር እንዲርቁ እጥራለሁ እነግራችቸዋለሁ።ሌላም ነገር ማድረግ ያለብኝን አደርጋለሁ። የሚገርም ነው! አሁን ሳይህ አስተሳሰብህ በጣም ወርቅ ነው ከዕድሜህ ጋር የሚመጣጠን አይደለም ... እስቲ ምንድነው ለወላጆች ልጆቻችንን በማሳደግ ውስጥ የምትመክረን ነገር አለ ለኢትዮጵያውያን ወላጆች ...... የኢትዮጵያ ወላጆች ልጆቻችሁን በጣም እንደምትወዱ እናውቃለን። በዚያ ምክንያት ልጆቻቸው መጥፎ ነገር ውስጥ እንዳይገቡ በጣም ስለሚያስቡና ስለሚጨነቁ ከአለምም ከማንም ጋር ብዙ እንዲገናኙ አይፈልጉም። እኔ ከተማርኩት በቃ you should let the kids be free እነሱም ወጥተው ያዩትና ከዚያ ይማራሉ። በኔ ሕይወት እንዳየሁት እንደዚያ ሆነው ካልተማሩ ከሰው ሲሰሙት ዝም ብሎ በቃ እንደ ተረት ነው የሚታያቸው። ደግሞ ብዙ ሰዎች ልጆችም ብቻ ሳይሆን ትላልቅም ሰዎች ቢሆኑ አታድርጉ የሚባሉትን ነገር ሁሉም ሰው ማድረግ ይፈልጋል። አድርገው ጥሩ እንዳልሆነ ራሳቸው አይተውት ከዚያ እንዲርቁ ማድረግ ነው እንጂ ገና ምንም ነገር ሳያዩ ከሆነ አይናችሁን ጨፍናችሁ ሂዱ እንደማለት ነው። የሚገርም ትልቅ አስተሳሰብ ነው! እኛ ከሁሉም ነገር ከልለንናችሁ ለዘላለም የምናኖራችሁ ይመስለናል ግን ለአለም መጋለጣችሁ አይቀርም ፤ እያዩት እየተረዱት ቢሄዱ ጥሩ ነው እያልከኝ ነው ማለት ነው? አዎ አለበለዚያ በድብቅ ነው የሚሆነው ሁሉም ነገር መጥፎ ነገር ይሆናል። ጓደኞች አፍርተሃል እዚህ? በጣም ብዙ
ናትናኤል ኢሳያስ ♦ ◊ ♦
◊
♦
◊
♦
◊ ♦ ◊ ♦
በየዓመቱ እስክታገኛቸው ትናፍቃቸዋለህ ? በጣም! ከዚህ ኮንፍራንስ ውስጥ ምንድነው ልብህን የሚማርከው ? አስተማሪዎችህ የመሳሰለው..... አስተማሪዎች ሁልግዜ ይለዋወጣሉ። መልዕክቱ ግን ሁሌም ይመጣል። ዋናው የሚመጣውን መልዕክት እኛ understand እንድናደርግ እስከረዱን ድረስ የእግዚአብሄር ነገር ይሰራል። ባንተ አስተሳሰብ ኮንፍራንሱን የሚያዘጋጁት መሪዎች ለወጣቶቹ ምን ነገር ቢያደርጉ ደስ ይልሃል? እ እ እ አሁን እያረጉ ያሉት ነገር ሁሉ ጥሩ ነው። ትንሽ መስተካከል አለበት የምለው like ብዙ organized አይሆንም አልፎ አልፎ ሰዓት እንድ ነገር ላይ ብዙ ግዜ ያጠፋሉ ወይም off topic ይሄዱና በትምህርት መካከል ላይ ግዜ እንዳይባክን control የሚያደርግ ሰው ቢኖር ጥሩ ይሆናል ብዬ አስባለሁ። እንዴት አድርጌ እንደማመሰግንህ አላውቅም ባንተ ወላጆችህን እያየሁ ነው ....ማን ይባላሉ ወላጆችህ? ኢሳያስና ማርታ ስንተኛ ልጅ ነህ ለቤተሰብህ? እኔ የመጀመሪያ ልጅ ነኝ። ናትናኤል በጣም ነው የመሰጥከኝ ጌታ አብዝቶ አብዝቶ ይባርክህ!
የኢትዮጵያ ወላጆች ልጆቻችሁን በጣም እንደምትወዱ እናውቃለን። በዚያ ምክንያት ልጆቻቸው መጥፎ ነገር ውስጥ እንዳይገቡ በጣም ስለሚያስቡና ስለሚጨነቁ ከአለምም ከማንም ጋር ብዙ እንዲገናኙ አይፈልጉም። ናትናኤል ኢሳያስ
ብዙ የማይነገረው የጌታ ዳግም ምፅዓት ውስጤ ውስጤር ...ብዙ ርቀርቷልል ቀርቷልል
ገ ጽ36
♦
ማን ልበል ስምሽን?
- አዎ
- ዘውድነሽ ታደሰ ♦
♦
ከየትኛዋ ቤ/ክ ነው የመጣሽው?
ልጆችስ አሉሽ?
◊
የፓስተር አሸናፊ ባለቤት ነኝ።
♦
ካንድ ሰው ጋር ስነጋገር በአንዳንድ ቤ/ክ ውስጥ ችግሮች ይነሳሉ በሚነሱበት ግዜ የፓስተር ሚስቶች የችግሩ አካል ከመሆን ይልቅ ችግሩን ለመፍታት ትልቅ ሚና ሊጫወቱ እንደሚችሉ ይነግረኝ ነበርና አንድ የአገልጋይ ባለቤት በዚህ በኩል ባሏን እንዴት መርዳት ትችላለች?
- አዎ
- ከኢትዮጵያ ወንጌላዊያን ኅብረት ቤ/ክ ካንሳስ
♦
ስንት ነው ዕድሜያቸው?
- የመጀመሪያ ልጄ 27 ዓመቷ ነው፤ ሁለተኛዋ 26 የመጨረሻዋ 14 ዓመቷ ነው
♦
ኮንፍራንሱ ላይ ይመጣሉ ?
- አዎ አገልጋዮች ናቸው ሁለቱ ልጆቼ፣ በሰንበት ትምህርት ቤት ያገለግላሉ።
♦
በእዚህ በ2011 ኮንፍራንስ ምንድነው ልብሽ ውስጥ የቀረ ነገር?
- በራሴ ሕይወት ባሳለፍኩት ብዙ ግዜ ባለቤቴን እፀልይለታለሁ። በፀሎት ብዙ እረዳዋለሁ። ባገልግሎቱ ውስጥ ጣልቃ መግባት አልፈልግም። ምክንያቱም አገልግሎት ትላንት እንደተባለው ልዩ ልዩ ነው። ጥሪያችን ልዩ ልዩ ነው። ከብዙ ክፉ ነገር ከማይሆን ነገር እግዚአብሔርን እንዲፈራ እመክረዋለሁ። ከዚህ በላይ ብዙም ማለት አልችልም።
- የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት፣ የእግዚአብሔርን ክብር ለማየት፣
- ልቤ ውስጥ የቀረው ትልቁ ነገር የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ♦ የጌታን ምፅዓት በመማርሽ እንደተባረክሽ ዳግም ምጽዓት ነው። ባሁኑ ዘመን ብዙ የማይነገር ትምህርት ነግረሽናል ግን ላንቺ በግልሽ የትኛው ስለሆነ ውስጤ ቀርቷል። እናም መቀደስ ነው። መዘጋጀት ፕሮግራም ነው ለኔ ልዩዬ ነው የምትይው? ነው! በተለይ የትላንትናው በጣም ልቤን ነክቶኛል -ትላንትና ማታ climax ነበር ለኔ I was really touched ፓስተር በድሉ በሚያስተምርበት ግዜ ♦ የትኛው? ማለቴ ነው ልቤ ተነክቷል። ዛሬም ጠዋት ወንድሞች አንዳች የፀጋ ስጦታ እንዳይጎድልባችሁ የሚለው ያ ብዙ ግዜ ሲያስተምሩ ዶ/ር መንግስቱም ሆነ ወንድማችን በፀጋ ስጦታዎች እያገለገልን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ፓስተር ገነቱ በዕውነት ልቤ ተነክቷል። እስካሁን መገለጥ መጠባበቅ እንዳለብን ትልቅ ትምህርት አግኝቻለሁ በነበረው ትምህርት ሁሉ ልቤ ተነክቷል። “እኔ ከዚያ ውስጥ። ብሄድ ይሻላችኋል... መንፈስ ቅዱስን እልክላችኋለሁ እሱም የእውነት መንፈስ ነውና ወደ ዕውነቱም ♦ የዚህን ኮንፍራንስ አዘጋጆች ምን ቢያሻሽሉ ነው ይመራችኋል” አለ ጌታ ። ያ የእውነት መንፈስ በቤ/ የምትመክሪያቸው? ክ ውስጥ ካልሰራ ስጋና ደም የእግዚአብሔርን ስራ - እኔ አንድ ያለኝ ሃሳብ ምንድነው እኔ ያገልጋይ ሚስት ነኝ ፣ ሊሰራው አይችልም። ያንን የበለጠ promote ባለቤቴ ፓስተር ነው ። ስለዚህ ከየቦታው የመጣነው የፓስተር ማድረጉ ለቤ/ክ ይጠቅማታል። ሚስቶች አንድ ላይ ሆነን የምንመካከርበት ግዜ ቢገኝ ፣ ♦ የዘንድሮ አስተናጋጅ የሒውስተን ቤ/ክ አንዳንዶቹ ባገልግሎት ረጅም ዘመን የቆዩ ሊሆኑ ይችላሉና ነች። ምን ትያለሽ ስለነሱ? አዲስ ለመጡትም መልዕክት ለመስጠት፣ እንዴት መሆን እንዳለብን ፣ እንዴት አድርገን መመላለስ እንደሚገባን፣ በዛ ጌታ ይባርካችሁ! ግሩም ነው ድንቅ ነው! አቅጣጫ የተወሰነ ግዜ ለፓስተሮቹ የሚዘጋጀውን ያህል እግዚአብሔር ይባርካችሁ! ተባረኩ! መጽሐፍ እንደዚሁ ለወንጌላውያንም፣ ለረዳት ፓስተሮችም ፣ ለሚስቶቻቸውም ቢዘጋጅና ብንመካከር ፣ አብረንም ብንፀልይ ቅዱስ “የእግዚአብሔር ስራ ይብዛላችሁ” ይላልና የእግዚአብሔር ስራ ይብዛላችሁ! ጥሩ ነው እላለሁ።
♦
♦
እህት ዘውድነሽ ታደሰ ♦
ምን ያህል ግዜ ሆኖሻል ኮንፍራንሱ ላይ ስትመጪ?
- ላለፉት 2 ዓመታት በስተቀር በየዓመቱ እመጣለሁኝ
♦
ምን ያህል ግዜ ይሆናል?
- አንድ ስድስት ሰባት ግዜ ሳይሆን አይቀርም በግምት!
♦
እንደዚህ ስድስት ሰባት ግዜ የሚያመላልስሽ ምንድነው ምክንያቱ?
ባለትዳር ነሽ ?
ይቅርታ ስላላወቅኩሽ የማን ባለቤት ነሽ?
እናመሰግናለን
የእግዚአብሔር ነገር የሚጠገብ የለውም .... ♦
ማን ልበል ስምሽን?
- ስሜ እስራኤል አበራ
♦
የት ነው የምትኖሪው?
-ዳላስ ቴክሳስ ♦
መቼ ነው ወደ አሜሪካ የመጣሽው?
- በ1999 ኖቬምበር ♦
ጌታን ካገኘሽ ምን ያህል ግዜ ሆኖሻል?
- እኔ ጌታን ያገኘሁበትን ዕድሜዬን አላውቀውም፣ በልጅነቴ ቤተሰቦቼ ክርስቲያኖች ናቸው ወደ ጌታ ከመታሁ ቆየሁ ምናልባት አንድ አስራ አምስት ዓመት ይሆነኛል። ♦
የት ነበር የምትኖሪው ሀገር ቤት ?
- እኔ የድሬዳዋ ልጅ ነኝ.. ጅቡቲም እኖር ነበረ። ♦
እህት እስራኤል አበራ
ስንተኛ ግዚሽ ነው እዚህ ኮንፍራንስ ላይ ስትመጪ?
- 8ኛ ግዜዬ መልሕቅ
♦
እዚህ ኮንፍራንስ ላይ የሚያመላልስሽ ምክንያት ምንድነው?
እዚህ ኮንፍራንስ ላይ ብዙ ነገር አለ ፣ ብዙ የእግዚአብሔር ፀጋ ፣ የእግዚአብሄር በረከት በተለያዩ የእግዚአብሔር ባሪያዎች የሚፈስ ብዙ መልካም ነገር አለ፤ ከቅዱሳኖች ጋር ብዙ ሕብረት ታደርጋለህ ፤ በጣም ደስ የሚል ነገር አለው። ያ ነው ምክንያቴ። ♦
የዘንድሮውን ኮንፍራንስ ከሌላው የሚለየው ምንድነው?
- ሁልግዜ እግዚብሔር አዲስ ነው! ብዙ አዳዲስና መልካም ነገር ይገኛል ከእግዚአብሔር ዘንድ። እኛ ተዘጋጅተን እንደመጣነው ልባችንን እንዳሰፋን የእግዚአብሔር ነገር ይገኛል። ሁሌ አዲስ ነው የእግዚአብሔር ነገር የሚጠገብ የለውም። የጌታ ነገር መልካም ነው!
ገ ጽ37
ማራናታ!
ላላገቡ የተሰጠን ትምህርት “ አይን ከፋች ነበር” ነበር” ዘንድሮ ይበልጥ ተባርኬበታለሁ የምትይው የትኛውን ፕሮግራም ነበር
♦
ሄደሽ ለሰው ሁሉ የምታወሪው ልብሽ ውስጥ የቀረ ፕሮግራም የትኛው ነው?
- ሁሉም መልካም ነው!
እንደው ልብሽ ውስጥ የቀረ ካለ ....
♦
- ልቤ ውስጥ የቀረው በርግጥ የትናንት ማታው “የእግዚአብሔር ፀጋ” የሚለው ፓስተር በድሉ ያገለገለው ምናልባት ፓስተሬ ስለሆነ አድልቼ እንደሆን አላውቅም .... ከአምልኮውስ ፕሮግራም?
♦
- በአምልኮው ፕሮግራም ሁሉም መልካም ግዜ ነበር። ከተጀመረ ጀምሮ እስካሁን መልካም ነው! እግዚአብሔር ይመስገን።
እህት ዕፀገነት ክፍሉ
ባለትዳር ነሽ?
♦
- ባለትዳርና የሶስት ልጆች እናት ነኝ። ማነው ልጆችሽ ስማቸው?
♦
- ልጆቼ ስማቸው ናትናኤል መላኩ ፣ ፅዮን መላኩ ፣ ባርሰነት መላኩ ዕድሜያቸውስ?
♦
- 10 ፣8 እና አንድ ዓመት ተኩል ልጆችሽ አብረውሽ መጥተዋል ፕሮግራም ይካፈላሉ?
♦
- አዎ! ♦
አሁን ወጣቶቹን ስናነጋግር “ ወላጆቻችችን ይወዱናል ግን በጣም ተጨንቀው ከሁሉ ነገር ፣ ከዓለም በሙሉ ሊከልሉን ይፈልጋሉ ይሄ ልክ አይደለም.....” ይላሉ ምን ያህል ዕውነት ነው ይሄ?
እኛ ትንሽ አልፈን አንሄድም?
- አዎ የባህልም ነገር ስላለ ፣ የማናውቀው culture ጋር ስላለን እንዳሉት ልንሆን እንችላለን... ♦
እስራኤል አበራ እጅግ እናመሰግናለን!
- ጌታ ይባርካችሁ!
የሒውስተን ቤተክርስቲያን ስለላከችልን ፎቶግራፎች ምስጋናችንን እናቀርባለን!
ማን ልበል ስምሽን?
- ዕፀገነት ክፍሉ ♦
የት ነው የምትኖሪው?
- ዳላስ ♦
አሜሪካ ከመጣሽ ምን ያህል ግዜ ሆነሽ
♦
- አስራ አንድ ዓመቴ ነው ♦
- ዕውነት ነው! ቤተሰብ ሁልግዜ ልጆቹን መጠበቅና ከክፉ ነገር ለመከላከል ግድ ነው። ♦
♦
- የተለየ ነገር የምለው ዕውነት ሁሉም የተለየ ነው። ከዚህ ሁሉ ግን ወደመጣንበት ስንመለስ በየእሁዱ የማናገኘውና ስፔሻል ሆኖ ያገኘሁት የወጣቶች ለወጣቶችና እንደገና ለልጆች አስተዳደግም የሆነ ትምህርት ነበረ አርብ ከሰዓት በኋላ ። የወጣቶቹ ያላገቡትን በተመለከተ በፓስተር እንድርያስ የተዘጋጀ ትምህርት ነበረ እጅግ በጣም ተደንቄያለሁኝ! በጣም ደግሞ ተምሬበታለሁኝ። በዕውነት ወጣቱ በዚህ በወጣትነት ዕድሜው ሳያገባ በፊት ሁላችንም ለማግባት ልባችን ይከፈታል። ነገር ግን ሳላገባ አሁን እንዴት ነው በጌታ ፊት የምመላለሰው? በእግዚአብሔር ሃሳብ ዘመኔ እንዴት ነው የሚዋጀው? እስካገባ ድረሥ እንዴት ልኑር?፣ ከዚያ በኋላ ራሴን እንዴት ነው ለትዳርም ሆነ ለአገልግሎት የማዘጋጀው? የሚለውን ነገር ፣እንደገናም ደግሞ የእግዚአብሔር ሀሳብ በትዳር ላይ ምንድነው? የእግዚአብሔር ሀሳብ በወጣትነት ዕድሜዬ ላይ ምንድነው? የሚለው ነገር አይን ከፋች ነበር ለኔ። አይኔን ነው የከፈተልኝ፣ እግዚአብሔርን በጣም አመሰገንኩኝ። ብዙ ትምህርቶችን ቀስሜያለሁ። በተረፈ ግን እንዳልኩት ኅብረቱ በጣም ልዩ ነው። ሁሉም ነገር amazing ነው!
ጌታን ካገኘሽስ?
- አንድ አስራ ስድስት አስራ ሰባት ዓመት ይሆነኛል ♦
ምን ያህል ግዜ እዚህ ኮንፍራንስ ላይ ተካፍለሻል?
- ይሄኛው ሁለተኛ ግዜዬ ነው ♦
ምን ዓይነት በረከት አገኘሽ?
- በጣም ! በጣም! ...ባለፈውም ዓመት በጣም ነበር የተነቃቃሁት፣ እንደዚህ ከሁኔታዎቻችን day to day basis (ከየዕለት) ኑሯችን ዕልፍ ብለን ፣ የእግዚአብሔርን ፊት ፈልገን፣ ሶስት ቀን ምንም በማይታይበት ነገር ግን የእግዚአብሔርን ምህረቱንና ቸርነቱን እያስተዋልን ፤ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር ደግሞ ጥሩ የሆነ የኅብረት ግዜ ሆኖልናል። ከሁሉ ከሁሉ በጣም የወደድኩት ከስምንት ቤ/ክ የተለያዩ የማንተዋወቅ ቅዱሳን ነገር ግን የእግዚብሔር ፍቅር አገናኝቶን አንድ ሆነን ጥሩ fellowship ግዜ ነበረን! ቃሉ ብቻ ሳይሆን fellowship ነበረን! እግዚአብሔር ይመስገን! ጌታን እጅግ አመሰግነዋለሁ! ደግሞ በዛም በጣም ተባርኬያለሁ። ክብር ለኢየሱስ ይሁን! ♦
ዘንድሮ የተለየ ነገር የምትይው ፣
የኮንፍራንሱ አዘጋጆች ምን ነገር ቢያሻሽሉ ትያለሽ?
- በዚህ ዝግጅት ላይ ቢያሻሽሉ የምለው… ይሄም ራሱ provide መደረግ ከሚገባው በላይ ነው! በብዙ ድካም ነው ...ቀላል አይደለም የብዙ ግዜ ዝግጅት እንደሆነ ያስታውቃል። ይሄንን ቢያሻሽሉ ብዬ ልል የምችለው ነገር ትንሽ provide ስላልተደረገ ይመስለኛል facility ስለሌለ ይመስለኛል የመኝታው ጉዳይ ጥሩ ሆኖ ሳለ ነገርግን ሰዎች ወደመኝታቸው ሲሄዱ advise ቢደረግ ጥሩ የዕረፍት ግዜ አድርገው ደግሞ ለማለዳው ፀሎት እንድንመጣ ያንን ያንን ቢያደርጉ ጥሩ ይመስለኛል። ግን ይሄ የአዘጋጆች አይመስለኝም። I mean እኔ ሁሉ ነገር ጥሩ ነው! ይሄን ያህል ብዙ ቢያስተካክሉ የምለው ነገር የለኝም። ♦
በኛ በኩል ጨርሰናል ባንቺ በኩል የምትይን ነገር ካለ?
- በዕውነት እግዚአብሔር አምላክ ያዘጋጁትንም ይባርክ! ሁላችሁንም እግዚአብሔር ይባርካችሁ! ተባርኬያለሁ! ክብሩን ሁሉ ደግሞ እግዚአብሔር ይውሰድ! በእውነት እኛ በመሰብሰባችን ብቻ ሳይሆን ልባችንን ባዘጋጀነው መጠን የእግዚብሔር መገኘት ዕለት ዕለት ሁሌ ይሁን ! እግዚአብሔር አምላክ አብዝቶ አብዝቶ ይባርካችሁ ማለት እፈልጋለሁ ለአዘጋጆቹ። ♦
ጌታ ይባርክሽ!
- አሜን አሜን!
ገ ጽ
38 38
ብሩኋ ታዳጊ ወጣት! ኮንፍራንስ ጨርሰን ወደ ሴንት ልዩስ የሚሄዱ ጥቂት የሒውስተን ቤተሰቦችን አሳፍረን እየተጓዝን ነው። መንገድ ላይ ዕረፍት እንዳደረግን አውቶቢሱ አካባቢ ቆሜ አንዲት ሕጻን ልጅ ስታልፍ አይቼ “ ሰላም!” አልኳት፤ አፀፋ አመላለሷ ፍፁም ቋንቋ እንደምትችል አስጠረጠረኝና ጠራኋት። እነሆ ጥርጣሬዬ ዕውነት ነበር ...
♦
ማነው ስምሽ?
♦
- በጣም!
♦
ምኑን ነው የወደድሽው?
ስንት ግዜ ሆነሽ ከኢትዮጵያ ከመጣሽ?
- አሁን ሰባተኛዬ ነው / ረስታዋለች አባቷ 5 ነው የሚለው /
- ሁሉንም
♦
♦
- ት/ቤት እንግሊዝኛ አወራለሁ እቤት ደግሞ አማርኛ አወራለሁ
እስቲ በጣም የወደድሽውን ነገር ንገሪኝ ?
አማርኛ እንዴት አልረሳሽም ?
- አምልኮውን
♦
♦
- ኖ እኔ የሄድኩበት Kindergarten እያለሁ ነው።
ዘማሪ አለ አዘማመሩን የወደድሽው
- ሁለቱንም
በአማርኛ መጻፍ ማንበብስ ትቺያለሽ? (ከሀገር ቤት የወጣሁት ለማለት ነው)
♦
አባትሽ የት ነው ያለው?
◊
አውቶቢስ ውስጥ )
- ዳንኤልና ጆሲ I mean ዮሴፍ
♦
ማነች እናትሽ?
♦
◊
ጊዜ ወርቅ
♦
ሌላስ ጓደኛ አገኘሽ ከሌላ ስቴት ?
ማነው ስማቸው? / ለልጆች
♦
የዘመሩላቸው ሌሎች ይኖራሉ ብዬ /
ዳንኤል አምደ ሚካኤልና ዮሴፍ?
- እህ
♦
ጎበዞች ናቸው?
- እህ ምስክርነት በአውቶቢስ ውስጥ
♦
ሌላስ ዘማሪ አላየሽም?
- አዜብ! / እንዴት ረሳኋት የምትል ትመስላለች/ - ቤርሲ / ቤርሳቤት ለማለት ነው/
♦
♦
- አላየሁም ሌላ
ስንት ዓመትሽ ነው?
- ዘጠኝ
♦
♦ ስንተኛ ክፍል ነሽ?
- አራት
♦
እርግጠኛ ነሽ?
ዶክተር ላሊን ታውቂዋለሽ
◊
አዎ
♦
ማነው ስማቸው?
◊
ቤቲ፣ ክሪስቺን፣ ዳዊት ፣ ሌላ ቤቲ፣ አቢጌል፣ ሌላ አቢጌል፣ ግሬስ የምትባል
♦
በጣም አመሰግናለሁ!
- አላውቀውም
♦
ኮንፍራንሱ ስንተኛሽ ነው?
ሲዘምር አላየሽውም? እዚህ እኛ አውቶቢስ ውስጥ አለልሽ እኮ
- ሁለተኛዬ
- አላየሁትም
♦
♦
ወደድሽው?
ከዶክተር ላሊ ጋር ተተዋወቁ
- አዎ
♦ የት ነው የምትኖሪው?
- ሒውስተን
♦
ሌላስ
ቆይ በኋላ አሳይሻለሁ
በልጆቹ የተባረከ አባት! -
♦
በሁሉ ነገር ዝግጅቱ ከመጀመሪያው እስከ አሁን ድረስ (ነገ የመጨረሻችን ነው) በጥሩ ሁኔታ እየተጠናቀቀ ነው ያለው።
ማን ልበል ስምህን?
- የሺጥላ ንጉሴ እባላለሁ።
♦
ከየትኛው ቤ/ክ ነህ?
♦
ያጋጠመ ችግር ነበር? - ምንም ያጋጠመን ችግር የለም፤ ያጋጠመን ችግር ቢኖር ሕፃናትን ከቤተሰባቸው ጋር ማገናኘት ነው።
♦
በዘንድሮው ኮንፍራንስ ምንድነው ልብህ ውስጥ የቀረልህ ነገር?
- በሒውስተን የኢትዮጵያውያኖች ኅብረት ቤ/ክ
♦
በቤ/ክ ውስጥ አገልጋይ ነህ?
- የቤ/ክ ሽማግሌ ነኝ።
♦
በዚህ ኮንፍራንስ ከዝግጅት ጀምሮ ፕሮግራሙን የምትመራልን የናንተ ቤ/ክ ነች በዚህ ውስጥ የተሰጠህ የስራ ድርሻ ምን ነበር ? ምን ነገር አየህ? - የተሰጠኝ የስራ ድርሻ የምግብ ቤት coordinator ወይም ደግሞ እንደ መሪ ሆኜ ከ8 ልጆች ጋር ነው ከሚድ ዌስት የመጡትን ክርስቲያኖች ሁሉ ያገለገልነው። ይሄ ኮንፍራንስ ከተጀመረ ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የታየው ጥሩ የሆነ ዝግጅት፣ ጥሩ የሆነ ምግብ ነበር። በተገልጋይነትም ጥሩ ስነምግባርና ስነ ስርዓት ያላቸው ምዕመናን ናቸው ያጋጠሙኝ
♦
ባለቤትህ ማን ትባላለች?
- ባለቤቴ አይናለም ታደሰ ትባላለች። እጅግ እናመሰግንሃለን! ስለ ግልጋሎታችሁ ጌታ አብዝቶ አብዝቶ ይባርካችሁ!
- ከዚህ ኮንፍራንስ የወሰድኩት ቁምነገር የክርስቶስ መምጫ ስለደረሰ ቤ/ክ ብቻ ሳትሆን እያንዳንዱ ምዕመን መዘጋጀት እንዳለበት ነው የተማርኩት።
♦
ቤተሰብ አለህ? - አዎ ቤተሰብ አለኝ።
♦
ስንት ልጆኦች አሉህ? - ሶስት ልጆች አሉኝ
♦
ምን ያህል ነው ዕድሜያቸው? ትምህርታቸውስ?
- ሁሉም እዚህ ናቸው። የመጀመሪያዋ 30 ዓመቷ ነው፤ የሚቀጥለው 28 ዓመቱ ነው፤ የመጨረሻዋ 22 ዓመቷ ነው። ሁለቱ ትምህርታቸውን ጨርሰው በስራ ላይ ነው ያሉት ፣ አንዷ next year ትመረቃለች።
ወንድም የሺጥላ ንጉሴ
ማራናታ!
ገ ጽ39
ከዳንኩ ከኦክላሆማ አልቀርም!
ተሽሎሽ ለኮንፍራንሱ ስትደርሺ የተሰማሽ ስሜት አለ? - የዘንድሮው የሚያነቃቃና ፣ ጌታን የምንጠብቅበት የማራናታ ጥቅስ ስለነበረ በጣም የተለየ አድርጎታል ። ይሄ ጉዳይ የደበዘዘ ነበረ እግዚአብሔር ይመስገን አሁን ተዘጋጅተን መኖር እንዳለብን ነው እሱ ነው የተለየ የሆነብኝ
♦
የትኛውን ፕሮግራም ነበር የበለጠ የወደድሽው? - ፕሮግራሞቹ ሁሉም ጥሩ ናቸው። በይበልጥ ግን የዶ/ር መንግስቱ ለማን ትምህርት ወድጄዋለሁ።
♦
♦
♦
♦
የዘንድሮው ኮንፍራንስ ላንቺ ምን የተለየ ነገር ነበረው?
ጌታን መቼ ነው ያገኘሽው? - ጌታን ያገኘሁት በልጅነቴ ነው!
♦
ምን ያህል ግዜ ይሆነዋል? - በልጅነቴ ነው ....(እ እ እ እያለች አሰበችና ሳቅ) ግን ሽርሽር ነበር በመሀከሉ። እንደዛ ነው። ዛሬም ነው ግን ጌታን ያገኘሁት። ዕለት ዕለት ነው እሱ ። ልዩ ነው!
ኦክላሆማ ኮንፍራንስ ምን ያህል ግዜ ተካፍለሻል? - እርግጠኛ አይደለሁም ወደ ሰባት ገደማ ይሆናል።
♦
♦
የየትኛው ቤ/ክ አባል ነሽ - የመድኃኒዓለም (ሳቅ) የሴንት ልዩስ ቤ/ክ አባል ነኝ።
የቤተሰብሽን ሁኔታ ብትገልጪልን
♦
ወደ ኮንፍራንስ ከመሄዳችን በፊት ታመሽ ሆስፒታል ነበርሽ። በግዜው
ለኮንፍራንሱ አዘጋጆች ምን ቢሻሻል የምትይው ነገር አለ? - የሚቀዱት ሲዲና ዲቪዲ ቢሻሻል ጥሩ ይመስለኛል። አንዳንድ ቤ/ክ ሰው ስለሚያበዙ አንዳንዶቹ ደግሞ በጥድፊያ ጥንቃቄ በጎደለው ሁኔታ ስለሚያደርጉት ይበላሻልና ቢታሰብበት መልካም ይመስለኛል።
የትኛውን?
- ባለ ትዳርና የ5 ልጆች እናት ነኝ።
ማን ልበል ስምሽን? - ገነት ላቀው ማርቆስ
♦
- ስለማራናታ ያስተማረውንና በሲስተም እንዴት እንደታሰርን ያስተማረው .....፣ አንደኛው ጠላታችን ቴሌቪዥን ነው የሚለው ነው ልቤን የነካው
ገነት ላቀው ወደ ኮንፍራንስ ጉዞ ላይ
♦
- በጣም የተሰማኝ ስሜት አለ። እኔ ከዳንኩ ከኦክላሆማ አልቀርም እያልኩ ነበር። “ አትችይም” እያሉኝ ነበር ቤተሰቦቼ። እግዚአብሔር እንዴት እንዳዘጋጀልኝ! ልክ ቴራፒውን የምጨርስበትና የማርፍበት ግዜ ነበር። ሐኪሞቹን እንኳን አልጠየቅኩም። እግዚአብሔር አዘጋጀልኝ! በሰላም ሄጄ በሰላም መጣሁ!
♦
የተለየ ጌታ የተናገረሽ ነገር አለ? - አዎ ጌታ ሳይናገር የሚቀርበት ግዜ የለም። እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን። በዘማሪ ዮሴፍ በቀለ በኩል “ያንቺ ነገር ተንከባሏል” ብሎኛል። እንግዲህ ጌታዬን እጠብቀዋለሁ። እንደቃሉ ያደርገዋል። ከአዘጋጁ፦ ከአዘጋጁ ያለፉት 4 ወራቶች ለቤተሰቧ የጭንቅ ግዜ ነበር። ለሰዓታት የፈጀ ቀዶ ጥገና ውስጥ አለፈች። የክትትል ሕክምናዋም ረጅም ግዜ የሚወስድ ነበር። ጨርሳ ሳታገግም የኦክላሆማ ኮንፍራንስ አያመልጥኝም ብላ አውቶቢሱ ስለማይመቻት መኪና ተከራይታ ከኮንፍራንሱ ተገኘች። ይሄም ተግባሯ የዚህን ኮንፍራንስ ተወዳጅነት በእጅጉ አሳየን።
የኪስ ቦርሳው ከገጽ 19 የዞረ አሰብን።፡እስቲ ድንገት ቦርሳዎን ጥለው እንደሆን ኪስዎን ይፈትሹ” አለቻቸው። አቶ ሚካኤል በመገረም እየተመለከቱን እጃቸውን ከኋላ ኪሳቸው ከከተቱ በኋላ “ አይ... ጥዬዋለሁ ማለት ነው!” አሉ። ለአቶ ሚካኤል ቦርሳውን ስሰጣቸው ገና ቦርሳውን ከማየታቸው በመገኘቱ ፋታ ፈገግ አሉና “ትክክል እራሱ ነው ! ቅድም ከሰዓት በኋላ ከኪሴ ወድቆ መሆን አለበት.... ስላገኝህልኝም ጉርሻ ልሰጥህ እወዳለሁ” አሉ። “አያስፈልግም ስለሃሳብዎ አመሰግናለሁ.... አንድ ነገር ግን ልነግርዎ እፈልጋለሁ የቦርሳውን ባለቤት ማን እንደሆን ለማወቅ ስል ደብዳቤውን አንብቤዋለሁ” አልኳቸው። በፊታቸው ላይ ይነበብ የነበረው ፈገግታ ከመቅጽበት ጠፋ። “ ይህን ደብዳቤ አነበብከው?” አሉ በቁጣ። “ ማንበብ ብቻ ሳይሆን ሃናም የት እንዳሉ አውቃለሁ” አልኳቸው። ፊታቸው ባንዴ ገረጣ “ሃና? የት እንዳለች ታውቃለህ? እንዴት ነች? እንደድሮዋ አሁንም ውብ ነች? እባክህ እባክህ ንገረኝ” በማለት ይለምኑኝ ገቡ።“ ደህና ናቸው አሁንም ልክ ያኔ እንደሚያውቋቸው ውብ ናቸው” አልኩኝ አለሳልሼ። ሽማግሌው እንደማውቅ በገመተ ፈገግታ “የት እንዳለች ልትነግረኝ ትችላለህ? ነገውኑ ልደውልላት እሻለሁ” .... ካሉኝ በኋላ እጄን ያዝ
አድርገው “ አንድ ነገር ልንገርህ ከዛች ልጅ ሃይለኛ ፍቅር ነበረኝ ይሄ ደብዳቤ ሲመጣ ሕይወቴ አከተመ መኖሬ አቆመ ። አላገባሁም። ምንግዜም እሷን እንደማፈቅራት ነው የሚሰማኝ” ሲሉኝ “አቶ ሚካኤል ይምጡ ከኔ ጋር” አልኳቸውና ወደሶስተኛ ፎቅ አሳንሳር ይዘን ወረድን። ኮሪደሩ ጨልሟል አንድ ሁለት የሌሊት መብራቶች ወደ መዋያ ክፍሉ መንገዳችንን አበሩልን። ወ/ሮ ሃና ብቻቸውን ተቀምጠው ቴለቭዥን ያዩ ነበር። ነርሷም ወደሳቸው ተጠግታ “ሃና” ብላ በቀስታ ተጣራች። በሩ መግቢያ ላይ ከኔ ጋር የቆሙትን አቶ ሚካኤልን በጣቶቿ እየጠቆመች “ እኝህን ሰው ያውቋቸዋል?” ስትል ጠየቀች። መነጽራቸውን እያስተካከሉ ለተወሰነ ግዜ አፈጠጡ።ቃል አልተነፈሱም። አቶ ሚካኤል በለስላሳና በሚያንሾካሽክ ድምጽ “ሃና ሚካኤል ነኝ ታስታውሽኛለሽ?” አሉ። ሃናም “ሚካኤል! እኔ አላምንም! ሚካኤል ዕውነት አንተ ነህ? የኔ ሚካኤል!” አሉ በሚያቃትት ድምጽ። ሚካኤል በቀስታ እየተራመዱ ወደ ሃና ሄደው ተቃቀፉ። እንኳን የነሀና እና ሚካኤል የእኔና የነርሷ እንባ በፊታችን ላይ ኮለል ብሎ ይወርድ ጀመር ።
ከሶስት ሳምንት በኋላ ከጡረተኞች ቤት ቢሮዬ ስልክ ተደውሎ “ እሁድ እለት መጥተህ የሰርግ በዓል ላይ ልትገኝልን ትችላለህ? ሚካኤልና ሃና በጋብቻ ሊተሳሰሩ ነው “ አሉኝ። ቆንጆ ሰርግ ነበር።የጡረተኞች ቤቱ ሰው በሙሉ በዓሉ ላይ ያማረ የሰርግ ልብሱን ግጥም አድርጎ ተገኝቷል። ሃና ብሩህ ሽሯማ ቯል ቀሚስ ለብሰው እጅግ ተውበዋል ። አቶ ሚካኤል ደማቅ ሰማያዊ ለብሰው ጎልተው ይታያሉ። ብቸኛ ሚዜያቸው አድርገውኛል። የጡረታ ቤቱ ለብቻቸው ክፍል ሰጥቷቸዋል። የ76 ዓመት ሙሽሪትና የ79 ዓመት ሙሽራ እንደ ሁለት ታዳጊ ወጣት ሲቦርቁ ማየት ከፈለጋችሁ እነኝህን ጥንዶች መመልከት አለባችሁ። ፍጻሜው ያማረ የ60 ዓመት የፍቅር ጉዞ። ከድረ ገጽ የተገኘ ተዛማጅ ትርጉም ብርሃኔ ሞገስ ጽጌ
ገ ጽ40
በፀሎትና በኑሮዋ ታታሪ እናት
ዳር ከዳር ( ቹቹ) መልሕቅ፦ መልሕቅ ማን ልበል ስምሽን? ቹቹ ፦ ዳርከዳር ብርሃኑ መልሕቅ፦ የየትኛዋ ቤ/ክ አባል ነሽ? ቹቹ፦ የሴንት ልዩስ መድኃኒዓለም መልሕቅ፦ መልሕቅ ምን ያህል ግዜ ነው እዚህ ኮንፍራንስ ላይ ስትካፈይ? ቹቹ፦ ከ17 ዓመት በፊት እካፈል ነበር። ነገር ግን ልጆች ከወለድኩ በኋላ ለረጅም ግዜ አልሄድኩም።
ቹቹ፦ ከሰዎችም ሆነ ከልጆች ጋር ለመግባባት አይቸግረውም ። ግን በጣም ቅብጥብጥ ነው። ዕረፍት የለውም። በጣም ይሮጣል ፤ ይጫወታል። አንዳንድ ነገሮች ለማጥፋት አንደኛ ነው ከልጆች ጋር ሆኖ። የጨዋታ ሰው ነው። በጣም ወደ ጨዋታ ያዘነብላል እንጂ ችግር የለውም። መልሕቅ፦ እናም 2011 ኦክላሆማ ኮንፍራንስ ልብሽን አሳርፎልሽ ነው የተመለሽው ማለት ነው? ቹቹ፦ ቹቹ አዎ! ምክንያቱም “እንዴት ይሆን ይሆን?” ፤ የሆነ ነገር ሆነ ቢባል በልጆች በኩል እሱ ይኖርበታል የሚል ሃሳብ እንዳይኖረኝ ነበር ፍርሃቴ። በዚህ ዓመት ምንም አላሰብኩም። መልሕቅ፦ አሁን አግኝቼው አናግሬው ነበር በት/ቤትም ፣ በቤ/ክም በቤትም ለውጥ አለኝ ። ከአስተማሪዎቼም ከትምህርቴም ጋር ባለኝ ግንኙነት እናቴም ትመሰክራለች ነው ያለኝና ትመሰክሪያለሽ?
ዳርከዳር ብርሃኑ (ቹቹ) በግምት በ13 ዓመት ውስጥ ለመጀመሪያ ግዜ ነው በዚህ ዓመት ስሄድ። መልሕቅ፦ ምስንት ልጅች አሉሽ? ቹቹ፦ ሁለት መልሕቅ፦ እስቲ ስለ ልጆችሽ ትንሽ ንገሪን? ቹቹ፦ ሁለቱም ልጆቼ ወንዶች ናቸው ። ሁለተኛው ልጄ 13 ዓመቱ ነው። ሁለት ልጅ ይዞ ኮንፍራንስ ለመሄድ በጣም ከባድ ነው። ከዚያ የተነሳ የመሄድ ነገሬን ያቀዘቀዘው ልጆቼ ሃይፐሮች ናቸው ። በጣም መሯሯጥ ስለሚወዱ ያስቸግራሉ የሚለው ነገር በጣም ስለሚያስጨንቀኝ የመሄድ ነገሬ በዚያ ምክንያት ቀርቷል። ግን አሁን በዚህ በ13 ዓመት ውስጥ አንደኛው ልጄ ሚልኪያስ ላይ በጣም የተለወጠ ነገር አያለሁኝ። ልቤን በዚያ ስላሳረፈኝ በዚህ ዓመት መሄድ አለብኝ ብዬ ወሰንኩ። አብሯቸው ካደጋቸው ከዳላስ ልጆች ጋር ማገናኘትም ስለፈለኩ ይዤው ሄድኩ። እሱም በጣም ደስ ብሎታል ። ያዩትም በጣም ተደስተዋል። ምክንያቱም ሚኪን የሚያውቁት በዚህ ዓይነት መልኩ ስላልነበረ ማለት ነው። ይሄም ሁኔታ የበለጠ ልቤን በእግዚአብሔር እንዳበረታ ረድቶኛል፤ ለሁለተኛው ልጄም ተስፋ ሆኖልኛል። ብዙዎች “ ይሄ ሚኪ ነወይ?” እስኪሉ ድረስ ተደንቀውበታል። በውስጡ የተረጋጋ ነገርና በመንፈሳዊም ሆነ በስጋዊ ብዙ ለውጦች እንዳዩበት ብዙዎች ነግረውኛል። እኔም አይቻለሁ። መልሕቅ፦ እስቲ አንዳንድ ነገሮች ንገሪን ምንድን ነበር ችግሩ? ከሰዎች ጋር ለመግባባት ይቸግረው ነበር? መልሕቅ
ቹቹ፦ አዎ! በተለይ በትምህርት ቤት ለኔ ብዙ ትዝታ አለኝ። ማለት መጥፎ ልጆች ክፍል ውስጥ ካሉ ከእነሱ ጋር በመሆን አስተማሪን ባለማክበርም ሆነ በተለያየ መንገድ የሚባለውንም ባለመስማት ፣ ት/ቤት ውስጥ አይታዘዝም ከሚባሉት ልጆች ውስጥ አንዱ ነበር። ባለፉት ሶስት አመቶች በፀባይ፣ በመታዘዝ ሽልማት ያገኛል። እንደውም አንድ አስተማሪው “ እንደ ሚኪ ዓይነት አስር ተማሪ ክፍሌ ውስጥ ቢገኝ ቤቴ አልመለስም ነበር” ብላ ልብ የሚነካ ነገር ነገረችኝ። በእውነትም ደግሞ ሳይ በብዙ መልኩ የመስማትና የማክበር የመታዘዝ ነገር በት/ቤት ውስጥ አለው። መልሕቅ፦ መልሕቅ ለዚህ ሁሉ ለውጥ ምክንያቱ ምን ይመስልሻል? ቹቹ፦ ይሄ የእግዚአብሔር ስራ ነው። ምክንያቱም እኔ እንኳን ለመፀለይ ቢደክመኝ፣ ብሰለች፣ ከእኔ ጋር አብረው በጣም በፀሎት የሚተጉና የሚያግዙኝ ፤ ስለ ልጆቼም ስለ እኔም የሚፀልዩ ወገኖች አሉኝ። የእነርሱ የፀሎት ፍሬ ነው። እኔም ደግሞ ስለ ልጆቼ ቀንም ሌሊትም እፀልያለሁ። እግዚአብሔር በሕይወታቸው ሊሰራ የጀመረው ነገር ነው። ይሄንን ያደረገው እሱ ነው ብዬ አምናለሁ። መልሕቅ፦ በዘንድሮው የኦክላሆማ ኮንፍራንስ ላይ ያገኘሽው የተለየ በረከት አለ? ቹቹ፦ አዎ! በተሰጡት ትምህርቶች በሙሉ እግዚአብሔር ተናግሮኛል። በጣም ልቤን ነክቶታል። በተለይ ፓስተር እንድርያስ ባስተማራቸው ትምህርቶች እራሴን እንዳይ ፣ የፀሎት ሕይወትና የመንፈስ ቅዱስ ስራ እንዴት እንደሆነ እንድገነዘብና የራሴን ሕይወት እንድመረምር ረድቶኛል። መልሕቅ፦ ስለ አምልኮው፣ ኅብረቱስ ምን ተሰማሽ ? ቹቹ፦ እኔ እንግዲህ እንደነገርኩህ ረዘም ላለ ግዜ ሰፋ ያለ ጉባኤ ላይ ሄጄ አላውቅም። ምክንያቴም ልጆቼ ናቸው። እንደዚያ ያለ ቦታ
እናትና ልጅ ከኮንፍራንስ መልስ ጉዞ ላይ
መሄድ ብዙ ነፃነት አይሰማኝም ነበር። እኔ ከዳላስ ከወጣሁ ወደ አምስት ዓመት ሆኖኛል ፤ ብዙዎቹ ጉባኤ ተካፋዮች ደግሞ ከዳላስ ናቸው፤ ሒውስተኖችንም አውቃለሁ፤ ከነዚህ ወገኖቼ ጋር መገናኘቴ ፣ ይሄንን ዕድል አግኝቼ በዚያ ጉባኤ አብሬ መካፈሌ ለኔ ትልቅ ነገር ነው ። ምክንያቱም ካለኝ ሁኔታ ብዙ የማይፈቅዱ ነገሮች አሉኝ። እግዚአብሔር ደግሞ ረድቶኝ ፣ ድልን ሰጥቶኝ በዚህ ሰዓት ከቅዱሳን ጋር ፣ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር በአንድ ጉባኤ ተሰብስቤ የእግዚአብሔርን ነገር እንድሰማ፣ እንድማር፣ እንድካፈልም ዕድል ስላገኘሁ በጣም ደስ ይለኛል። ሕዝቡን በማየቴ ትልቅ ደስታ ተሰምቶኛል። መልሕቅ፦ አመሰግናለሁ!
የቹቹ ልጅ የሚልኪያስ ቃል(ትርጉም) ........ተለውጫለሁ። መፅሐፍ ቅዱስ በየቀኑ አነባለሁ። እፀልያለሁ። ስበላም እፀልያልለሁ። እነዚህን ነገሮች በፊትም አደርግ ነበር። አሁን ግን ከእግዚአብሔር ጋር የበለጠ በመቅረብ፣ በቋሚነት ነው የማደርጋቸው። ስለ ጌታ ኮምፕዩተሬ ላይ አነባለሁ። ምድር ላይ በነበረበት ግዜ የነበረውን ታሪክ አጠናለሁ።...... ......አስተማሪዎቼን አከብራለሁ፣ ለልጆች ስለ ጌታ እናገራለሁ። ጌታ እንደሚወዳቸውም እነግራቸዋለሁ ........እኔና እናቴ አብረን መፅሐፍ ቅዱስ እናነባለን፤ እንፀልያለን ፣ በጌታ ምክንያት የተሻለ ግንኙነት ነው ያለን። እናቴ “ ይሄን አድርግ፣ የቤት ስራህን ስራ” ትለኝ ነበር። ላደርገው አልፈልግም ነበር። አሁን ግን አደርገዋለሁ ማድረግ ብቻም አይደለም በትክክል አደርገዋለሁ። ግዜዬን ወስጄ አነባለሁ፣አጠናለሁ፤ የበለጠ እዘጋጃለሁ ፣ ስንፍና የለም። .......ኦክላሆማ የአካካቢው ሁኔታ፣ ሰላማዊ ነበር፤ ሰዎቹ ለእግዚአብሔር የተሰጡ ነበሩ ፣ ለጨዋታም፣ ለመወያየትም፣ ለመብላትም፣ አምላክን ለማምለክም ለመፀለይም ፣ለሁሉም ነገር ግዜ ነበረን። ሰዎች ይተባበራሉ ፤ እዚያ የነበርነው ለሌላ ጉዳይ አልነበረም እግዚአብሔርን ለመፈለግ እንጂ.......
ማራናታ!
ገ ጽ41
የነገዋ ዶክተር ♦
ስንተኛ ክፍል ነሽ?
- አሁን 12ኛ ክፍል ነኝ። ♦
የት ነው የተወለድሽው?
- የተለየ የማደርገው የ 2009 ነው። ( አዘጋጇ የሴንት ልዩስ ቤክ ስለነበረች ይመስላል)
♦
- የተወለድኩት ኢትዮጵያ ፣ ባህር ዳር ነው። ♦
መቼ መጣሽ ወደ አሜሪካ?
- 2006 ላይ ነው የመጣሁት። ♦
ከስንተኛ ክፍል ነው የመጣሽው?
- 6ኛን ልጨርስ ስል ነው የመጣሁት ♦
ራሄል ዓለሙ ጥላሁን
♦
ማን ልበል ስምሽን?
- ስሜ ራሄል ዓለሙ ጥላሁን ይባላል። ♦
የት ነው የምትኖሪው?
- ሴንት ልዩስ ሚዙሪ ነው የምኖረው። ♦
ማነው የቤተክርስቲያንሽ ስም
- የቤተክርስቲያኔ ስም መድኃኒዓለም ወንጌላዊት ቤ/ክ ይባላል። ♦
በዘንድሮው የሚድ ዌስት ኮንፍራንስ ምን የተለየ በረከት አግኝተሻል?
- ሁልግዜም አዲስ አዲስ በረከት አለ። አንተ መጀመሪያ ልብህን አዘጋጅተህ መሄድ አለብህ። ልባችንን ካላዘጋጀን አዲስ ነገር ተቀብለን አንመጣም። በዚህ ዓመት ሁሉም ነገር የተለየ ነበር I guess እኔም ልቤን አዘጋጅቼ ስለሄድኩኝ ጌታ የፈለኩትን ነገር ሰጥቶኛል። እንደገና.. ♦
ለምሳሌ?
- ስለ ትምህርቴ ጥያቄ ነበረኝ። ምን ማድረግ እንዳለብኝ፣ ለወደፊቱ ምን መሆን እንደምፈልግ፣ እፀልይ ነበር በጣምና ጌታ ሆይ መልስ እፈልጋለሁ ስል ነበርና እዚያ ሄጄ ጌታ እንደተናገረኝ መልሴ እንደተመለሰ ነው..
አማርኛ መጻፍ ማንበብ ትችያለሽ?
- ሳቅ በደንብ ነው የምችለው! ( እንዴት ብትንቀኝ ነው ይሄን የምትጠይቀኝ የምትል ትመስላለች )
ዘንድሮ ከተማርሻቸው ትምህርቶች ውስጥ የትኛው ነበር በተለይ የመሰጠሽ? ካምልኮ ግሩፖችስ?
- የአምልኮ ግሩፕ ለወጣቶች የነበረው አንድ ብቻ ነው። የመሰጠኝ የጥያቄና መልሱ ፕሮግራም ነበር። ፓስተሮቹ ሁሉም ተቀምጠው ወጣቶቹ የሚያልፉበትን ነገር፣ የትኛው ነው ሐጢያት ? የትኛው ነው ሐጢያት ያልሆነው የሚል እንደዛ አይነት ጥያቄ እንድንጠይቅ ዕድል ሰጥተውን ነበር። ዘማሪዎቹና ፓስተሮቹ ያለፉበት ስለነበረ የነሱን experience ይነግሩን ነበርና እሱኛው በጣም ደስ ይል ነበር። ከአዋቂዎቹጋ ቃል የተካፈልኩት ጋሽ ታዲዮስና ፓስተር ገነቱ ሲያስተምሩ ነበር በጣም ጥሩ ነበር።
ስንት ሰዓት ነው ተጉዘሽ ኮንፍራንሱጋ ኮንፍራንሱ ላይ የተሳተፍሽው ከወጣቶች ♦ የደረሽው? ጋር ነው ወይስ ካዋቂዎች ጋር? - ከ12 ሰዓት በላይ ሳቅ አውቶቢሱ ለመተኛት - ሁለቱምጋ ተካፍያለሁ። አይመችም በጣም ደክመን ነበር። ስንሄድ እንኳን ♦ የትኛው ፕሮግራም ነው የተለየ ሆኖ ጉጉት ስለነበረን ምንም አይመስልህም ስንመለስ ግን በነጋታው ትምህርት መጀመር ነበረብንና ያገኘሽው? በጣም ድክም ብሎን ነበር። - እኔ ያደግኩት በአበሻው ስታይል ስለሆነ ፣ የአባሻ መዝሙር እየሰማሁ ስለሆነ የበለጠ ልቤን ♦ ስለ ኦክላሆማ ስታስቢ መጀመሪያ በደንብ የሚነካኝ የአበሻው ነው። ከህፃንነቴ አዕምሮሽ ውስጥ የሚመጣው ጀምሮ ያደግኩበት ስለሆነ ያ ነው የሚስበኝ። ምንድነው? እንግሊዝኛውም በጣም ደስ ይላል። second - መጀመሪያ የሚመጣው ነገር ከሁሉ ነገር ግልል language ስለሆነ እንደ first language እርክት ማለትህ! ስልክ የለም፣ ኢንተርኔት የለም ፣ ቲቪ አትልበትም። የለም፣ አለማዊ ጓደኞችህ የሉም፣ ከሁሉ ነገር ነፃ ♦ የአምልኮው ፕሮግራም እንዴት ነበር? ሆነህ ከጌታ ጋር ትነሳለህ። ሁሉ ነገር የምታስበው ስለ ጌታ ነው። - አምልኮው በጣም ደስ ይላል። የመጀመሪያው ቀን የእንግሊዝኛው አምልኮ በዳላስ worship ♦ ወደፊት ምን ለመሆን ነው team የተዘጋጀውም በጣም ደስ ይል ነበር። የምትፈልጊው? በጣም ጎበዞች ጌታ የባረካቸው ናቸው። - አሁን ወደ ኮሌጅ ስሄድ medicine ነው የአዋቂዎቹም በጣም ደስ የሚል ነበር። ለመማር የማስበው እንግዲህ ዶክተር ነው ♦ ምን ያህል ግዜ ተሳትፈሻል? የምሆነው። ♦
- I think 4ኛ ግዜዬ ነው። ♦
የትኛውን ኮንፍራንስ ነው የተለየ የምታደርጊው?
♦
ስለቤተሰብሽ ትንሽ ነገሪን፣ ስንተኛ ልጅ ነሽ?
- ለቤተሰቤ 3ኛ ልጅ ነኝ። ትልቅ እህትና ትልቅ ወንድም አለኝ ፣ ትንሽ እህትም አለችኝ።
ከሰባኪው ትዝታ! ትዝታ ዶ/ር መንግስቱ ለማ ስለ ማራናታ ሲሰብክ የልጅነት ትዝታው ትውስ አለውና እንዲህ አለ .... “አምቦ ነበር ያለነው፣ ወደ ገጠር ተገብቶ የእሁድ ገበያ የሚባል ቦታ አለ። እዚያ ተሄዶ እሁድ እሁድ ወንጌል ይሰበካልና ተሰብስበን ሄድን ...አንዱ ሰባኪ ያካባቢውን የታወቀ ቃልቻ ስም እየጠራ “....የሰይጣን አገልጋይ ነው! እንዲህ ያደርጋችኋል !” እያለ ሲሰብክ ......አንድ የታወቁ አቶ ኢራን ጋታ የተባሉ ባላባት ጉዳዩ ስላናደዳቸው ተከታዮቻቸውን አስከትለው በዱላ እየደበደቡ አሳደዱን። ሮጠን መኪናችን ውስጥ ገብተን ወደ አምቦ ስንመለስ መዝሙሩ ደመቀ ፤ መድመቅ ብቻ አይደለም “ ድልን እንድናገኝ ሁላችን እንበርታ” የሚለው ቃል ተቀይሮ ትንቢት ተፈፀመ መምጣቱ ነው ጌታ ዱላ ይዞ መጣ አቶ ኢራን ጋታ” እያልን .....ከማለቱ አዳራሹ በሳቅ ፈነዳ
(በኮንፍራንሱ ወቅት ለረጅም ሰዓት የተሳቀበት ታሪክ አዘል ቀልድ ) ዶ/ር መንግስቱ ለማ የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ጉባኤ መሪ
ገ ጽ42
ከካሜራችን ማኅደር ማኅደር
በእውነትና በመንፈስ አምልኮ
ወጣቶች ባምልኮ ላይ
መልሕቅ
የመልሕቅ ቀን በኦክላሆማ
ምግብ ቤታችን
ገ ጽ43
ማራናታ!
ዘማሪ ዳንኤል እና አዜብ ከየልጆቻቸው ጋር
የ2011 ሚድ ዌስት ኮንፍራንስ አስመላኪዎች
ተጋባዥ ዘማሪ ዮሴፍ በቀለ በማስመለክ ላይ
ዓውደ ጥናት የትዳር ጓደኛ እንዴት ልምረጥ?
በፓስተር እንድርያስ ሐዋዝ
የልጆች አስተዳደግ
የ18ኛው የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ኮንፍራንስ አዘጋጅ የሒውስተን የኢትዮጵያውያን ኅብረት ቤ/ክ አባላት
ሕይወታችን የሚድ ዌስት አብያተ ክርስቲያናት ታዳጊ ወጣቶች ፣ ሕፃናትና ወጣቶች